Showing posts with label የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት. Show all posts
Showing posts with label የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት. Show all posts

Friday, February 20, 2026

❖የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት:-

የአዲስ ኪዳን ጥናት በቅኝት መልክ
አዲስ ኪዳን ማለት አዲስ ውል አዲስ ስምምነት ማለት ነው፡፡ ለምን አዲስ ኪዳን ተባለ ስንል ፊተኛውን ኪዳን አስረጅቶ ስለገባና የዘላለም ኪዳን ስለሆነ ነው (ዕብ. 8፥13፤ 1፥1-2)፡፡ እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር አዲስ ኪዳን እንደሚገባ አስቀድሞ በነቢያት ተናግሯል (ኤር. 31፥31-34፤ ዕብ. 8፥8-13)፡፡ ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን ሲነጻጸሩ አዲሱ ኪዳን ብልጫ አስገኝቷል፡፡ ብሉይ ኪዳን ባሰጣጡ ጊዜያዊ ሲሆን አዲስ ኪዳን ግን ዘላለማዊ ነው (ማቴ. 11፥13፤ ሉቃ. 16፥16)፡፡ ብሉይ ኪዳን የተሰጠው በሙሴ መካከለኛነት ሲሆን አዲስ ኪዳን ግን በእግዚአብሔር ልጅ መካከለኛነት ተሰጥቷል (ገላ. 3፥19፤ 1ጢሞ. 2፥5)፡፡ ብሉይ ኪዳን ሕዝቡን ሊያድን ስላልቻለ የኲነኔ አገልግሎት ነበረ፤ አዲስ ኪዳን ግን የሕይወት አገልግሎት ነው (2ቆሮ. 3፥7-11)፡፡ ብሉይ ኪዳን በድንጋይ ላይ የተጻፈ የሕግ ግዴታ ሲሆን አዲስ ኪዳን ግን በልባችን ጽላት ላይ የተጻፈ የፍቅር ሕግ ነው (2ቆሮ. 3፥3)፡፡
የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሰባት በሚያህሉ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት የተጻፈ የሃያ ሰባት መጻሕፍት ጥቅልል ናቸው፡፡ እነዚህ ደቀ መዛሙርት መንፈስ ቅዱስ እስኪያድርባቸው ጌታን ይከተሉ የነበረው ለምድራዊ ትልቅነት ነበር፡፡ ነገር ግን ክርስቶስ ሞትን አሸንፎ ከተነሣና መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ከምድራዊ የክብር አሳብ ተላቀው ሁሉን ጥለው ተከተሉት፡፡ ወንጌሉንም በማይመቹ ሁኔታዎች ለዓለም አደረሱ፡፡ መልእክቶቹን የጻፉት በርቀት የነበሩትን ክርስቲያኖች በእምነታቸው ለማጽናት ነው፡፡ የመልእክቱ ባለቤት መንፈስ ቅዱስ ግን እኛን ጭምር በዚያ መልእክት ውስጥ ይመለከት ነበር፡፡
አዲስ ኪዳን እንደ ብሉይ ኪዳን ሁሉ የራሱ የሆነ አከፋፈል አለው፡፡ ስለዚህ በአራት ተከፍሎ ይጠናል፡፡ ወንጌል፣ ታሪክ፣ መልእክትና ትንቢት፡፡
                                ወንጌል
ወንጌል የሚባለው ከማቴዎስ እስከ ዮሐንስ ያሉት አራት ክፍሎች ናቸው፡፡ እነዚህ ክፍሎች የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መጸነስ፣ መወለድ፣ መኖርና መሞት፣ ትንሣኤና ዕርገት በሙሉነት ስለሚተርኩ ወንጌል የሚለውን ስያሜ አግኝተዋል፡፡ ወንጌል ማለት ክርስቶስን ማዕከል ያደረገ መልእክት ነው (ሮሜ. 1፥3-4)፡፡ ወንጌል ቃሉ ዩአንገሊዎን ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ነው፡፡ ትርጉሙም የምሥራች ቃል ወይም የድኅነት ዜና ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ተወልዶ በመስቀል ላይ ስለ ኃጢአታችን ሞቶ ዓለምን ማዳኑን ስለሚናገርና ፍርድን የሚጠባበቁ ኃጢአተኞች ተስፋ ስለመጣላቸው ወንጌል ወይም የምሥራች ቃል ተብሏል፡፡
አራቱ ወንጌላት ቀጥተኛ ግባቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ድኅነት የሚጠይቀውን ሙሉ መንገድ ተጉዞ የሰውን ዘር ከዘላለም ጥፋት ማዳኑ ነው፡፡ ፀሐፊዎቹም ሁለቱ ማለትም ማቴዎስና ዮሐንስ ከጌታ አሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት መካከል ሲሆኑ ሁለቱ ደግሞ ማርቆስና ሉቃስ ከሐዋርያት ጋር በቅርበት የነበሩ ከእነርሱ የሰሙትን በጥንቃቄ የጻፉ ናቸው፡፡ የማቴዎስ፣ የማርቆስና የሉቃስ ወንጌላት ተመሳሳይ ትረካ ያላቸው ሲሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው መሆኑን በመግለጥ እግዚአብሔር በሰውና በሰው ታሪክ መካከል ያደረገውን ይተርካሉ፡፡ ዮሐንስ ግን በተለየ ሁኔታ የኢየሱስ ክርስቶስን ዘላለማዊ ክብር በመግለጥ አምላክነቱን ሰዎች እንዲቀበሉት ይጥራል፡፡ ቢሆንም ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ተገልጦ ያደረገው ተአምርና የተናገረው ቃል ሰማይ ብራና፣ ዕፅዋት ሁሉ ብዕር፣ ውቅያኖስ ሁሉ ቀለም ቢሆኑ ተጽፎ አያልቅም (ዮሐ. 21፥25፤20፥30)፡፡ ለመዳናችን የሚበቃን ግን ተጽፎልናል፡፡


አራቱ ወንጌላት
የማቴዎስ ወንጌል፡- በአዲስ ኪዳን ውስጥ ብዙ ምዕራፍ ካላቸው ሁለት መጻሕፍት አንዱ የማቴዎስ ወንጌል ነው፡፡ ማቴዎስ ወንጌሉን የጻፈው ለአይሁድ ስለሆነ የዘር ሐረግን፣ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን በብዛት ይጠቅሳል፡፡ አይሁድ መሢሑን እንዲቀበሉ መሢሑ የአብርሃምና የዳዊት ዘር መሆኑን የሚገልጥ የዘር ፍሰትን ያወሳል፡፡ ለማስረጃም የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን በብዛት ይጠቅሳል፡፡ በዘር ሐረጉ ግን አይሁድ የማይጠቀሙበትን ስልት በመጠቀም አራት ሴቶችን ጠቅሷል (ማቴ. 1፥4 ቁ. 5.6.16)፡፡ አይሁድ በዘር ሐረግ ውስጥ ሴቶችን አስገብተው አይቆጥሩም ነበርና፡፡ ክርስቶስ ግን የመምጣቱ አንዱ ዓላማ ይህን ልዩነት ለማስወገድ ነበር፡፡
የማርቆስ ወንጌል– ከወንጌላት ትንሽ ምዕራፎች ያሉት የማርቆስ ወንጌል ነው፡፡ የትምህርቱም ስልት የክርስቶስን የእጁን ተአምራት በመግለጥ በዘመኑ የነበሩ ሮማውያንን ለማሳመን ነው፡፡ ጌታችን በተያዘ ሌሊት እርቃኑን በነጠላ ሸፍኖ ይከተለው ነበርና በያዙት ጊዜ ነጠላውን ትቶ ራቁቱን የሸሸው ወጣት ማርቆስ መሆኑን ብዙ ሊቃውንቶች ይናገራሉ (ማር. 14፥51-52)፡፡ እናቱ ቤቷን ለአገልግሎት በመልቀቋ የማርቆስ እናት ቤት የመጀመሪያይቱ ቤተ ክርስቲያን የሚል ስያሜ አግኝታለች (ሐዋ. 12፥12-17)፡፡ ማርቆስ ከበርናባስ፣ ከጳውሎስና ከጴጥሮስ ጋር ብዙ ጊዜ አገልግሏል፡፡ የጴጥሮስም የመንፈስ ልጁ ነው (1ጴጥ. 5፥13)፡ ወንጌሉን የጻፈውም ከእነዚህ ሐዋርያት በጥልቀት በመጠየቅና በማዳመጥ ነው፡፡
የሉቃስ ወንጌል፡- ሉቃስ ከአሕዛብ ወገን የሆነና በክርስቶስ ያመነ የጳውሎስም ደቀ መዝሙር የሆነ ሰው ነው፡፡ በሙያውም ሐኪም እንደ ነበረ ተጠቅሷል (ቈላ. 4፥14)፡፡ ስለ ክርስቶስም ሙሉ ትረካ ያቀረበ ፀሐፊ ነው፡፡ ወንጌሉን የጻፈው ከአሕዛብ ወገን ለነበረና ላመነ ቴዎፍሎስ ለሚባል ወዳጁ ነው፡፡ ማቴዎስ ወንጌሉን ከዘር ሐረግ ይጀምራል፣ ማርቆስ ከጥምቀቱ ይጀምራል፣ ሉቃስ ግን የኢየሱስ ክርስቶስ መልእክተኛ ከሆነው ከዮሐንስ መጥምቅ የጽንሰት ዜና ይጀምራል፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሉቃስ ወንጌሉንና የሐዋርያት ሥራን ጽፎአል፡፡
የዮሐንስ ወንጌል፡- ዮሐንስ ወንጌላዊ ከሦስቱ ወንጌላት በተለየ ሁኔታ ወንጌሉን ጽፎአል፡፡ ሦስቱ ወንጌላውያን የኢየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆንና ሰብአዊ ቅርበቱን ተርከዋል፡፡ ዮሐንስ ደግሞ የክርስቶስን መለኮታዊ ክብር በማጉላት ጽፎአል፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰውነትና ፍጹም አምላክነት መቻቻል አለባቸው፡፡ ሰውነቱ አምላክነቱን ጋርዶብን አምልኮ እንዳንነፍገው፣ አምላክነቱ ሰውነቱን ሸፍኖብን እንዳናርቀው መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ የወንጌላውያኑም ጭንቀት ይህ ነው፡፡ ዮሐንስ በአዲስ ኪዳን ውስጥ አንድ ወንጌል፣ ሦስት መልእክታት፣ አንድ የራእይ መጽሐፍ ጽፎአል፡፡
ታሪክ
በአዲስ ኪዳን የታሪክ ክፍል ተብሎ የሚጠራው አንድ ጥራዝ ብቻ ነው፡፡ እርሱም የሐዋርያት ሥራ ነው፡፡
የሐዋርያት ሥራ፡- የሐዋርያት ሥራን የጻፈው ሉቃስ ነው፡፡ የጻፈውም ወንጌልን ለጻፈለት ቴዎፍሎስ ለተባለው ወዳጁ ነው፡፡ በሉቃስ ወንጌል እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ሲናገር የሐዋርያት ሥራ ደግሞ ከዕርገቱ በኋላ ስላሉት ዐሥር ቀኖችና ስለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ ይናገራል፡፡ የመጽሐፉ ሙሉ ይዘት ወንጌል ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም ከዚያም እስከ መላው ዓለም በእንዴት ያለ ጸጋና ዋጋ መድረሱን የሚተርክ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አድሮ የሠራው ሥራ በመሆኑ የሐዋርያት ሥራ ቢባልም ታሪኩን ስንዘልቀው ግን “የመንፈስ ቅዱስ ሥራ” ቢባል መልካም ነበር ያሰኛል፡፡ በዚህ መጽሐፍ በስፋት የተገለጠው የጴጥሮስና የጳውሎስ አገልግሎት ነው፡፡ መጽሐፉ እንደ ሌሎቹ መልእክታት በሰላምታ ወይም በምርቃት አይዘጋም፡፡ ይህ የሚያስረዳን የሐዋርያት ሥራ በትውልድ ሁሉ መቀጠሉን ነው፡፡
መልእክት
የአዲስ ኪዳን ሦስተኛው አከፋፈል መልእክት ነው፡፡ መልእክት የሚባሉት ከሮሜ እስከ ይሁዳ ድረስ ያሉት 21 የመጻሕፍት ጥቅልል ናቸው፡፡ ፀሐፊዎቹም ጳውሎስ፣ ጴጥሮስ፣ ዮሐንስ፣ ያዕቆብና ይሁዳ ናቸው፡፡ የተጻፉትም ለግለሰቦችና ለአብያተ ክርስቲያናት ነው፡፡
የጳውሎስ መልእክታት
ከሮሜ እስከ ዕብራውያን ድረስ ያሉት ዐሥራ አራት መልእክቶች ጳውሎስ የጻፋቸው መልእክቶች ናቸው፡፡ ጳውሎስ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት መካከል አይደለም፡፡ ጌታ ካረገ ከስምንት ዓመት በኋላ ነው የተጠራው፡፡ ክርስትናን በብርቱ ይቃወም በነበረ ሰዓት በደማስቆ መንገድ በመብረቅ ብርሃን ጥሎት፣ ሦስት ቀን ዓይኑን አውሮት በወንጌል አመነ (የሐዋ. 9፥18)፡፡ ከሁሉ ኋላ የተጠራ ቢሆንም ከሐዋርያት ይልቅ ሮጧል፣ ዋጋ ከፍሏል፣ አብያተ ክርስቲያናትን መሥርቷል፣ መልእክታትን ጽፏል፡፡ በመጨረሻም በ67 ዓ.ም በሮም አደባባይ በሰይፍ ሞቷል፡፡ መልእክቶቹ ግን ከከዋክብት ደምቀው በዓለም ሁሉ በየዕለቱ ያበራሉ፡፡ መልእክታቱ የተጻፉት ለግለሰቦችና ለአብያተ ክርስቲያናት ሲሆን ምእመናንን ለማጽናት፣ ለመገሰጽ፣ ለማጽናናት፣ ቤተ ክርስቲያንን ፍሬያማ ለማድረግ ባጠቃላይ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመንና በማወቅ ለማደግ ተጽፈዋል፡፡ ጳውሎስ መልእክታቱን የጻፈው ከእስር በፊትና በእስር ዘመን ነው፡፡ መልእክታቱም አብያተ ክርስቲያናቱ በሚገኙበት አገርና ግለሰቦች ተሰይመዋል፡፡ ለምሳሌ፡- የሮሜ መልእክት ሮም ለምትገኘው ቤተ ክርስቲያን የተጻፈ ሲሆን የጢሞቴዎስ መልእክት ደግሞ የጳውሎስ የመንፈስ ልጅ ለሆነው ለኤፌሶኑ ጳጳስ ለጢሞቴዎስ የተጻፈ ነው፡፡
የጴጥሮስ መልእክታት
ጴጥሮስ ከኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት አንዱና የመጀመሪያው ሲሆን የኢየሱስ ክርስቶስን የእጁን ተአምራት፣ የቃሉን ትምህርት በቀጥታ የተቀበለ ነው፡፡ ጳውሎስ የአሕዛብ ሐዋርያ ሲሆን ጴጥሮስ የአይሁድ ሐዋርያ ነበር፡፡ በ67 ዓ.ም በሮም አደባባይ የቊልቊሊት ተሰቅሎ እስኪሞት በብዙ ስደትና መከራ ወንጌልን ሰብኮአል፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሁለት መልእክታትን ጽፎአል፡፡ የመጀመሪያው መልእክቱ በተለያዩ የእስያ አውራጃዎች ስለ ወንጌል ለተሰደዱ ክርስቲያን አይሁዶች የጻፈው ሲሆን በመታገሥ ያለውን ሰማያዊ ዋጋ በመግለጥ ሊያጸናቸው ጽፏል፡፡ ሁለተኛይቱ የጴጥሮስ መልእክት ደግሞ በክርስቲያኖች መካከል ሰርገው ስለገቡ የሐሰት መምህራን (መናፍቃን) ምእመናን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጽፎአል፡፡ ለቤተ ክርስቲያን የአረማውያን ነገሥታትን ያህል የሐሰት መምህራንም ጎጂዎቿ ናቸውና፡፡
የዮሐንስ መልእክታት
ዮሐንስ የክርስቶስን መለኮታዊ ክብር ለማጉላት ወንጌሉን እንደ ጻፈ  ዓይተናል፡፡ ደግሞም ሦስት መልእክታትንም አዘጋጅቷል፡፡ መልእክታቱንም ሆነ ወንጌሉን እንዲሁም ራእዩን የጻፈው በዕድሜው መጨረሻ አካባቢ ነው፡፡ የመጀመሪያይቱን መልእክቱን የጻፈው በዘመኑ ተስፋፍቶ የነበረውን የመናፍቃንን እንቅስቃሴ ለመጋፈጥና ምእመናን በፍቅር እየተባበሩ እምነታቸውን እንዲጠብቁ ለማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛይቱን መልእክት ደግሞ የጻፈው ለአንዲት አማኝ ሴት ሲሆን ከስህተት ትምህርት እንድትጠበቅ ነው፡፡ ሦስተኛይቱ የዮሐንስ መልእክት በቤቱ እንግዶችን ለሚቀበል ጋይዮስ ለተባለ በጎ አማኝ ለምስጋና የጻፈለት መልእክት ነው፡፡
የያዕቆብ መልእክት
ያዕቆብ ከጌታ ደቀ መዛሙርት አንዱ ነው፡፡ ይህ ያዕቆብ ይህችን ቀደምት መልእክቱን የጻፈው በስደት ለተበተኑት ክርስቲያን አይሁድ ሲሆን የመልእክቱ ዋና ዓላማ በመከራቸው እንዲፀኑና እምነታቸውን በምግባር እንዲገልጡ ለማነቃቃት ነው፡፡
የይሁዳ መልእክት
ባለ አንድ ምዕራፍ ከሆኑት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት አንዱ የይሁዳ መልእክት ሲሆን ይሁዳም መልእክቱን የጻፈው በስም ላልተጠቀሱ አማንያን ነው፡፡ የመልእክቱም ዓላማ ክርስቲያኖች ሁሉ እምነታቸውን እንዲጠብቁ ለማስጠንቀቅ ነው፡፡
ትንቢት
በአዲስ ኪዳን ውስጥ የትንቢት መጽሐፍ ተብሎ የሚጠራው የዮሐንስ ራእይ ነው፡፡
የዮሐንስ ራእይ፡- ዮሐንስ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ተግዞ /ታስሮ/ ሳለ በራእይ ያለፈውን፣ ያለውንና የሚመጣውን ተገልጾለት ጽፏል፡፡ የዮሐንስ ራእይ ክርስቲያኖችን ለማይቀረው የክርስቶስ ምጽአት ያዘጋጃል፡፡ አገላለጹም ሥዕላዊ ነው፡፡ ይህ የሆነው ሥዕል ከብዙ ቃላት ይልቅ የመናገር አቅም ስላለውና ዳግመኛም መጽሐፉን ከአደጋ ለመከላከል ነው፡፡ ትንቢቶቹ በግልጽ ቢጻፉ ኖሮ አረማውያን ነገሥታት በቶሎ ይጠፉታልና ጠላት ለመቀነስ ነው፡፡
ይህንን ጥናት ስናጠና የመጽሐፍ ቅዱሳችንን ማውጫ እየተመለከትን ብናጠና ይበልጥ ይብራራልናል፡፡ አንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በምዕራፍ ይከፈላል፡፡ ምዕራፉ ደግሞ በቊጥር ይከፈላል፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሲጠቀስ በአጭሩ ይጠቀሳል፡፡ ለምሳሌ፡- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ አሥራ አምስት ቊጥር ስድስት ቀጥሎ ባለው መልኩ ይጠቀሳል፡- (ዘፍ. 15፥ 6)፡፡

Thursday, February 19, 2026

❖የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት:-

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በቅኝት መልክ

መጽሐፍ ቅዱስ ማለት “ልዩ መጽሐፍ” ማለት ነው፡፡ በዓለም ላይ ከሚገኙት መጻሕፍት ልዩ የሚያደርገው በእግዚአብሔር መንፈስ የተጻፈና ሕይወት ሰጪ መጽሐፍ በመሆኑ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የኪዳን መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሕዝቡን የሚመራው በኪዳኑ መሠረት ነው፡ ከእያንዳንዱ ሰው ጋርም ኅብረት የሚያደርገው በኪዳን ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ የኪዳኑ ቅዱስ ሰነድ ነው፡፡ እነዚህም ታላላቅ ኪዳናት ሁለት ሲሆኑ ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን ይባላሉ፡፡ ኪዳን የሚያሟላቸውን ነገሮች ቀጥሎ ባለው ሠንጠረዥ ተገልጿል፡፡
ኪዳኑ
ኪዳን ሰጪ
ኪዳን ተቀባይ
የኪዳን ግዴታ
የኪዳን በረከት
የኪዳን ምልክት
ብሉይ ኪዳን
እግዚአብሔር
እስራኤል
ሕግን መጠበቅ
ከነዓንን መውረስ
ሰንበት
አዲስ ኪዳን
እግዚአብሔር
በክርስቶስ ያመኑ ሁሉ
እምነት
የዘላለም ሕይወት
ቅዱስ ቊርባን
       
የሰንጠረዡ ማብራሪያ ፡- በሁለቱም ኪዳናት የኪዳኑ ባለቤትና ኪዳን ሰጪ እግዚአብሔር ነው (ኤር. 31፥31-34፤ ዕብ. 8፥8-12)፡፡ የመጀመሪያው ኪዳን (ብሉይ ኪዳን)  የተሰጠው ለአንድ ሕዝብ (ለአይሁድ) ሲሆን አዲስ ኪዳን ግን የተሰጠው ለመላው ዓለም (ላመኑት ሁሉ) ነው (ዘፀ. 24፥1-8፤ዮሐ. 3፥16)፡፡ ብሉይ ኪዳን የሕግ ግዴታ ሲኖረው አዲስ ኪዳን ደግሞ በክርስቶስ ማመንን ይጠይቃል (2ቆሮ. 3፥4-18፤ ገላ. 2፥16)፡፡ የብሉይ ኪዳን በረከቱ ምድራዊ ሲሆን  የአዲስ ኪዳን ግን ሰማያዊ በረከት ነው (ኢያ. 1፥1-9፤ ኤፌ. 1፥3)፡፡ ኪዳን ማስታወሻ /ምልክት/ ያስፈልገዋል፡፡ የብሉይ ኪዳን ምልክቱ ሰንበት ሲሆን በአዲስ ኪዳን ግን ቅ/ቊርባን ነው (ዘፀ. 31፥17፤ ሉቃ. 22፥20)፡፡

የሁለቱ ኪዳናት ሰንሰለት
        ሁለቱ ኪዳናት ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን እንደማያቋርጥ የወንዝ ፈሳሽ፣ አንዱ አንዱን እንደሚስበው ሐረግ፣ አንደኛው በአንዱ እንደ ታሠረ ሰንሰለት የታሪክና የእምነት ትስስር አላቸው፡፡ አንዱ ያለ አንዱ እንደማይቆም የሕንጻ   ካብ ሁለቱ ኪዳናት ተደጋግፈዋል፡፡ ብሉይ ኪዳን ጅምር ሲሆን አዲስ ኪዳን ፍጻሜ ነው፡፡ ብሉይ ኪዳን ያለ አዲስ ኪዳን መጨረሻ የሌለው መጀመሪያ ነው፡፡ አዲስ ኪዳንም ያለ ብሉይ ኪዳን መጀመሪያ የሌለው መጨረሻ ነው። ስለዚህ ስብከታችን ከብሉይ ኪዳን ተነሥቶ ወደ አዲስ ኪዳን ሲመጣ ዘላለማዊነትን ያገኛል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የኪዳናቱን ትስስር ጥላና አካል፣ ምሳሌና እውነት፣ ትንቢትና ፍጻሜ እያለ ይገልጠዋል (ቈላ. 2፥16፤ ዕብ. 10፥1፤ ሉቃ. 24፥44)፡፡
የብሉይ ኪዳን ጥናት በቅኝት መልክ
        ብሉይ ኪዳን ማለት ምን ማለት ነው? ስንል ብሉይ ማለት በግእዝ ቋንቋ አሮጌ /ያረጀ/ ማለት ነው፡፡ ኪዳን ማለት ደግሞ መሐላ፣ ውል ስምምነት ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ብሉይ ኪዳን ማለት የቆየ መሐላ ማለት ነው (ዕብ. 8፥13)፡፡ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በአራት ይከፈላሉ፡፡ እነርሱም፡-
   ኦሪት
   ታሪክ
   ጥበብና
   ትንቢት ይባላሉ፡፡
ኦሪት
        ኦሪት ማለት ሕግ ማለት ነው፡፡ የኦሪት መጻሕፍት የሚባሉትም ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ኦሪት ዘዳግም ያሉት አምስት መጻሕፍት ናቸው፡፡ ፀሐፊያቸውም ሙሴ ነው፡፡
ኦሪት ዘፍጥረት፡- “ዘ” የሚለው የግእዝ ፊደል “የ” የሚለውን የአማርኛ ቃል የሚተካ አገናኝ ቃል ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ማለትም “የመፈጠር ሕግ” ማለት ነው፡፡ የኦሪት ዘፍጥረት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ምዕራፎች ስለ ዓለምና ስለ ሰው ተፈጥሮ ስለሚናገሩ ከሦስቱ የመግቢያ ምዕራፎች አሳብ በመነሣት ኦሪት ዘፍጥረት ወይም የመፈጠር ሕግ የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡
ኦሪት ዘፀአት፡- “የመውጣት ሕግ” ማለት ነው፡፡ የእስራኤል ልጆች ከግብጽ ባርነት ነጻ መውጣታቸውን ስለሚተርክ የመውጣት ሕግ ተብሏል።
ኦሪት ዘሌዋውያን፡- “የሌዋውያን ሕግ” ማለት ነው። ሌዋውያን የመቅደስ አገልጋዮች ናቸው። መጽሐፉ ስለ ሌዋውያን አገልግሎት ስለሚናገር የሌዋውያን ሕግ ተብሏል። መልእክቱ ቅድስናን የሚመለከት በመሆኑም “የቅድስና ሕግ” ይባላል። ትልቁ የአገልግሎት መገለጫም ቅድስና ስለሆነ ኦሪት ዘሌዋውያን መባሉ መልካም ነው።
ኦሪት ዘኁልቍ፡- “የመቆጠር ሕግ” ማለት ነው። የእስራኤል ልጆችን እንዲቆጥር እግዚአብሔር ሙሴን ያዘዘበት ክፍል ስለሆነ የመቆጠር ሕግ ተብሏል፡፡
ኦሪት ዘዳግም፡- “የመደገም ሕግ” ማለት ነው፡፡ ሙሴ በምድረ በዳ ለተወለዱት የእስራኤል ልጆች የሕጉን መጽሐፍ እንደገና ስላስተማራቸው የመደገም ሕግ ተባለ፡፡ በክፍሉ ላይ ሙሴ ከግብጽ ምድር ለወጡት የእግዚአብሔርን ውለታ ሲያዘክር፣ በምድረ በዳ ለተወለዱት ደግሞ ትእዛዙን ይከልስላቸዋል፡፡
ታሪክ
የታሪክ ክፍል የሚባለው ከመጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ እስከ መጽሐፈ አስቴር ያሉት 12 መጻሕፍት ናቸው፡፡
መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ፡- የነዌ ልጅ የኢያሱ መጽሐፍ ማለት ነው፡፡ የነዌ ልጅ ኢያሱ ከሙሴ ቀጥሎ እስራኤልን የመራና የተስፋቸው ፍጻሜ የሆነችውን ከነዓንን ያከፋፈለ መሪ ነው፡፡ ፀሐፊው እርሱ ስለሆነም መጽሐፉ በስሙ ተሰይሟል፡፡
መጽሐፈ መሳፍንት፡- ከኢያሱ ሞት በኋላ 13 መሳፍንት እስራኤልን አስተዳድረዋል። እግዚአብሔር ሕዝቡን በመሳፍንት አድሮ ከጠላት እንዴት እንደታደጋቸው የሚገልጽ መጽሐፍ ነው። ሳሙኤል እንደጻፈውም ይገመታል።
መጽሐፈ ሩት፡- በሴት ስም ከተሰየሙት ሁለት መጻሕፍት አንዱ መጽሐፈ ሩት ነው፡፡ ሩት ከዚህም ሌላ አሕዛባዊት ሴት ስትሆን በእግዚአብሔር ጥበብ የዳዊት የሴት ቅድመ አያት ለመሆን በቅታለች፡፡ ፀሐፊው ሳሙኤል እንደሆነ ይነገራል፡፡
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊና ካልዕ፡- እነዚህ በታላቁ ነቢይ በሳሙኤል የተሰየሙት ሁለት መጻሕፍት ከመሳፍንት ዘመን ማብቂያ ጀምሮ ያለውን ዘመነ ነገሥትን ይተርካሉ፡፡ ሰፊ ሽፋንም የተሰጣቸው የመጀመሪያው ንጉሥ ሳኦልና ሁለተኛው ንጉሥ ዳዊት ናቸው፡፡ ቀዳማዊ ማለት አንደኛ ማለት ሲሆን ካልዕ ማለትም ሁለተኛ ማለት ነው፡፡ የእነዚህ መጻሕፍት ፀሐፊ ሳሙኤል ስለሆነ በእርሱ ስም ተሰይመዋል፡፡
መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊና ካልዕ፡- ከሦስተኛው ንጉሥ ከሰሎሞን እስከ ባቢሎን ምርኮ የነገሡትን የ360 ዓመታት የነገሥታት ታሪክ የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፈ ነገሥት ተብሏል፡፡ ፀሐፊው ማን እንደሆነ አልታወቀም፡፡ 
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊና ካልዕ– ዜና መዋዕል ማለት የዘመናት ታሪክ ማለት ነው፡፡ ከመጽሐፈ ነገሥት ጋር ሙሉ በሙሉ የዘመን ትስስር አለው፡፡ ወይም አራቱም መጻሕፍት የተወሰኑ ዘመናትን በጣምራነት ይተርካሉ፡፡ ልዩነቱ ግን የነገሥት ሁለት መጻሕፍት የቤተ መንግሥቱን ታሪክና ውድቀት ሲተርኩ የዜና መዋዕል መጻሕፍት ግን የቤተ ክህነቱን ሂደትና ውድቀት ይተርካሉ፡፡ አራቱም መጻሕፍት እስከ ባቢሎን ምርኮ ድረስ ዘግበዋል፡፡ የዜና መዋዕል መጻሕፍትም ዕዝራ እንደ ጻፋቸው ይነገራል፡፡
መጽሐፈ ዕዝራ፡- ዕዝራ ፀሐፊና ካህን ነበር፡፡ በባቢሎን ምርኮ ያደገ ሰው ነው፡፡ ቤተ መቅደሱ እንዲሠራና ሕዝቡም መንፈሳዊ መነቃቃት እንዲያደርግ የታገለ ሰው ነበር፡፡ ፀሐፊውም ራሱ ስለሆነ መጽሐፈ ዕዝራ ተብሏል፡፡
መጽሐፈ ነህምያ፡- ነህምያ በባቢሎን ምርኮ አገር የንጉሡ ጠጅ አሳላፊ ነበር፡፡ ስለ ኢየሩሳሌም መፍረስ ስለ ቅጥርዋ መናድ አብዝቶ ያዝን ነበርና በንጉሡ ፈቃድ ቅጥርን አደሰ፣ አስተዳደርዋንም መለሰ፡፡ መጽሐፉን ራሱ ነህምያ ስለ ጻፈው በስሙ ተሰይሟል፡፡
መጽሐፈ አስቴር፡- አስቴር በምርኮ አገር ንጉሡን ያገባች ሴት ስትሆን ወገኖቿ አይሁድ የታወጀባቸውን የሞት አዋጅ እንዲቀይር በቆራጥነት የደከመች ሴት ናት፡፡ አይሁድም የሞት አዋጁ በሕይወት ተለውጦላቸዋል፡፡ በሴት ስም ከተሰየሙት ሁለት መጻሕፍት አንዱ መጽሐፈ አስቴር ነው፡፡ ፀሐፊው ማን እንደሆነ አልታወቀም፡፡ አይሁድ ከሞት የዳኑበትን ቀን “ፉሪም” ዕጣ ማለት ነው ሲያከብሩ መጽሐፈ አስቴርን ያነቡ ነበር፡፡
ጥበብ
የጥበብ መጻሕፍት የሚባሉት ከመጽሐፈ ኢዮብ እስከ መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ድረስ ያሉት አምስት መጻሕፍት ናቸው፡፡
መጽሐፈ ኢዮብ፡- በጥንት ዘመን ስለኖረና በሕይወት ብዙ ተፈትኖ ነጥሮ ስለወጣው ስለ ኢዮብ የሚናገር መጽሐፍ ሲሆን መጽሐፉም በራሱ በኢዮብ ተሰይሟል፡፡ ፀሐፊው ማን እንደሆነ አልተገለጸም፡፡
መዝሙረ ዳዊት፡- ነቢዩና ንጉሡ ዳዊት ስለ ሕይወቱ ስለ ኑሮው ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገው ንግግር ነው። ደራሲውም የመዘምራን አለቃ ዳዊትና ሌሎችም ዘማርያን ናቸው።
መጽሐፈ ምሳሌ፡- የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌ ነው፡፡ ሰሎሞን ሦስት መጻሕፍትን አዘጋጅቷል፡፡ መጽሐፈ ምሳሌ፣ መጽሐፈ መክብብ፣ መኃልየ መኃልየ ዘሰሎሞን ይባላሉ፡፡ መክብብ ማለት ሰባኪ ማለት ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ውጭ ስላለው ነገር ከንቱነት ይናገራል፡፡ መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ማለት ደግሞ ከመዝሙሮች የሚበልጥ የሰሎሞን መዝሙር ማለት ነው፡፡ በሁለት ሰዎች ማለት በሴትና በወንድ ቅላፄ የተዋቀረ መዝሙር ሲሆን የቤተ ክርስቲያንና የክርስቶስን ፍቅር ይገልፃል፡፡
ትንቢት
የትንቢት ክፍሎች ዐሥራ ሰባት መጻሕፍትን ይዘዋል፡፡ ነቢያቱ አንዳንዴ በሁለት፣ ሌላ ጊዜም በሦስት ይከፈላሉ፡፡ በሁለት ሲከፈሉ ዐበይት ነቢያትና ደቂቅ ነቢያት ይባላሉ፡፡ ስለዚህ ዐበይት ነቢያት የሚባሉት ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ፣ ሕዝቅኤልና ዳንኤል ናቸው፡፡ ደቂቅ ነቢያት የሚባሉትም ከሆሴዕ እስከ ሚልክያስ ያሉት ነቢያት ናቸው በሦስት ሲከፈሉም ከምርኮ በፊት የነበሩ፣ በምርኮ ዘመን የነበሩ፣ ከምርኮ ዘመን በኋላ የነበሩ ነቢያት ተብለው ይከፈላሉ፡፡
   ከምርኮ ዘመን በፊት የነበሩ፡- ኢሳይያስ፣ ሆሴዕ፣ አሞጽ፣ ሚክያስ፣ ኢዩኤል፣ አብድዩ፣ ዮናስ፣ ናሆም፣ ዕንባቆም፣ ሶፎንያስ፣ ናቸው፡፡
   በምርኮ ዘመን የነበሩ፡- ኤርምያስ፣ ሕዝቅኤል፣ ዳንኤል ናቸው፡፡
   ከምርኮ ዘመን በኋላ የነበሩ፡- ሐጌ፣ ዘካርያስና ሚልክያስ ናቸው፡፡
ከምርኮ ዘመን በፊት የነበሩት ነቢያት ሕዝቡን ይገስጹ፣ ያስጠነቅቁ ነበር፡፡ በምርኮ ዘመን የነበሩ ነቢያት ደግሞ ሕዝቡን ያጽናኑ ነበር፡፡ ከምርኮ ዘመን በኋላ የነበሩ ነቢያት ደግሞ የፈረሰው እንዲጠገን፣ የእግዚአብሔር ቤት እንዲለማ ያበረታቱ ነበር፡፡ ከትንቢት ክፍሎች ትርጉም የሚያሻው አርእስት “ሰቆቃወ ኤርምያስ” ሲሆን ትርጉሙም የኤርምያስ ሐዘን ወይም ልቅሶ ማለት ነው፡፡
የብሉይ ኪዳን ሠላሳ ዘጠኙ መጻሕፍት ከ1400-400 ዓመተ ዓለም ከክርስቶስ በፊት ተጽፈዋል፡፡ የመጨረሻውም ነቢይ ሚልክያስ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ባሉት ዓመታት ውስጥ የተጻፉ መጻሕፍትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ እና የካቶሊክ ቤ/ክ ተቀብለዋቸዋል፡፡ እነዚህ መጻሕፍት ዲዩትሮካኖኒካል ወይም ተጨማሪ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት አሊያም “የብሉይ ኪዳን 2ኛ የቀኖና መጻሕፍት” በመባል የሚታወቁት ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት ከ39ኙ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ጋር በአንድነት የተቆጠሩት ከሰባ ሊቃናት ትርጉም በኋላ ነው፡፡ ሰባ ሊቃናት የሚባሉት ለመጀመሪያ ጊዜ ብሉይ ኪዳንን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ የተረጎሙ የአይሁድ መምህራን ናቸው፡፡ እነዚህ ሊቃውንት ብሉይ ኪዳንን ወደ ግሪክ ሲመልሱ እነዚህንም መጻሕፍት አብረው መልሰዋል፡፡ መጻሕፍቱ በጥንቱ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ይሰጡ ነበር፡፡ ከባቢሎን ምርኮ በኋላ እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ስላለው የታሪክ ሂደት እነዚህ መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ የምክርና የጥበብ ትምህርቶችንም ይዘዋል፡፡ ለምሳሌ፡- መጽሐፈ ሲራክንና መጽሐፈ ጥበብን መጥቀስ እንችላለን፡፡
በርግጥ የአይሁድ መምህራን (ረቢዎች) በ90 ዓ.ም. በምዕራብ ኢየሩሳሌም ያምኒያ በሚባለው ቦታ የያምኒያ ጉባዔ ተብሎ በሚጠራው የሊቃውንት ስብሰባ እነዚህን መጻሕፍት እንደማይቀበሉ ውሳኔ አሳልፈዋል፡፡ መጻሕፍቱ ግን በኦርቶዶክስና በካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት ተቀባይነት አግኝተዋል፡፡ እንግዲህ የብሉይ ኪዳን ቀጥተኛ ተቀባዮችና ባለ አደራዎች አይሁዳውያን ሲሆኑ የአዲስ ኪዳን ቀጥተኛ ተቀባይና ባለ አደራ ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡

Thursday, March 16, 2017

❖የአዲስ ኪዳን ጥናት በቅኝት መልክ

አዲስ ኪዳን ማለት አዲስ ውል አዲስ ስምምነት ማለት ነው፡፡ ለምን አዲስ ኪዳን ተባለ ስንል ፊተኛውን ኪዳን አስረጅቶ ስለገባና የዘላለም ኪዳን ስለሆነ ነው (ዕብ. 813 11-2)፡፡ እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር አዲስ ኪዳን እንደሚገባ አስቀድሞ በነቢያት ተናግሯል (ኤር. 3131-34 ዕብ. 88-13)፡፡ ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን ሲነጻጸሩ አዲሱ ኪዳን ብልጫ አስገኝቷል፡፡ ብሉይ ኪዳን ባሰጣጡ ጊዜያዊ ሲሆን አዲስ ኪዳን ግን ዘላለማዊ ነው (ማቴ. 1113 ሉቃ. 1616)፡፡ ብሉይ ኪዳን የተሰጠው በሙሴ መካከለኛነት ሲሆን አዲስ ኪዳን ግን በእግዚአብሔር ልጅ መካከለኛነት ተሰጥቷል (ገላ. 319 1ጢሞ. 25)፡፡ ብሉይ ኪዳን ሕዝቡን ሊያድን ስላልቻለ የኲነኔ አገልግሎት ነበረ፤ አዲስ ኪዳን ግን የሕይወት አገልግሎት ነው (2ቆሮ. 37-11)፡፡ ብሉይ ኪዳን በድንጋይ ላይ የተጻፈ የሕግ ግዴታ ሲሆን አዲስ ኪዳን ግን በልባችን ጽላት ላይ የተጻፈ የፍቅር ሕግ ነው (2ቆሮ. 33)፡፡

የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሰባት በሚያህሉ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት የተጻፈ የሃያ ሰባት መጻሕፍት ጥቅልል ናቸው፡፡ እነዚህ ደቀ መዛሙርት መንፈስ ቅዱስ እስኪያድርባቸው ጌታን ይከተሉ የነበረው ለምድራዊ ትልቅነት ነበር፡፡ ነገር ግን ክርስቶስ ሞትን አሸንፎ ከተነሣና መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ከምድራዊ የክብር አሳብ ተላቀው ሁሉን ጥለው ተከተሉት፡፡ ወንጌሉንም በማይመቹ ሁኔታዎች ለዓለም አደረሱ፡፡ መልእክቶቹን የጻፉት በርቀት የነበሩትን ክርስቲያኖች በእምነታቸው ለማጽናት ነው፡፡ የመልእክቱ ባለቤት መንፈስ ቅዱስ ግን እኛን ጭምር በዚያ መልእክት ውስጥ ይመለከት ነበር፡፡
አዲስ ኪዳን እንደ ብሉይ ኪዳን ሁሉ የራሱ የሆነ አከፋፈል አለው፡፡ ስለዚህ በአራት ተከፍሎ ይጠናል፡፡ ወንጌል፣ ታሪክ፣ መልእክትና ትንቢት፡፡
                                ወንጌል

ወንጌል የሚባለው ከማቴዎስ እስከ ዮሐንስ ያሉት አራት ክፍሎች ናቸው፡፡ እነዚህ ክፍሎች የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መጸነስ፣ መወለድ፣ መኖርና መሞት፣ ትንሣኤና ዕርገት በሙሉነት ስለሚተርኩ ወንጌል የሚለውን ስያሜ አግኝተዋል፡፡ ወንጌል ማለት ክርስቶስን ማዕከል ያደረገ መልእክት ነው (ሮሜ. 13-4)፡፡ ወንጌል ቃሉ ዩአንገሊዎን ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ነው፡፡ ትርጉሙም የምሥራች ቃል ወይም የድኅነት ዜና ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ተወልዶ በመስቀል ላይ ስለ ኃጢአታችን ሞቶ ዓለምን ማዳኑን ስለሚናገርና ፍርድን የሚጠባበቁ ኃጢአተኞች ተስፋ ስለመጣላቸው ወንጌል ወይም የምሥራች ቃል ተብሏል፡፡

አራቱ ወንጌላት ቀጥተኛ ግባቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ድኅነት የሚጠይቀውን ሙሉ መንገድ ተጉዞ የሰውን ዘር ከዘላለም ጥፋት ማዳኑ ነው፡፡ ፀሐፊዎቹም ሁለቱ ማለትም ማቴዎስና ዮሐንስ ከጌታ አሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርት መካከል ሲሆኑ ሁለቱ ደግሞ ማርቆስና ሉቃስ ከሐዋርያት ጋር በቅርበት የነበሩ ከእነርሱ የሰሙትን በጥንቃቄ የጻፉ ናቸው፡፡ የማቴዎስ፣ የማርቆስና የሉቃስ ወንጌላት ተመሳሳይ ትረካ ያላቸው ሲሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው መሆኑን በመግለጥ እግዚአብሔር በሰውና በሰው ታሪክ መካከል ያደረገውን ይተርካሉ፡፡ ዮሐንስ ግን በተለየ ሁኔታ የኢየሱስ ክርስቶስን ዘላለማዊ ክብር በመግለጥ አምላክነቱን ሰዎች እንዲቀበሉት ይጥራል፡፡ ቢሆንም ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ተገልጦ ያደረገው ተአምርና የተናገረው ቃል ሰማይ ብራና፣ ዕፅዋት ሁሉ ብዕር፣ ውቅያኖስ ሁሉ ቀለም ቢሆኑ ተጽፎ አያልቅም (ዮሐ. 21252030)፡፡ ለመዳናችን የሚበቃን ግን ተጽፎልናል፡፡

                                     አራቱ ወንጌላት

የማቴዎስ ወንጌል- በአዲስ ኪዳን ውስጥ ብዙ ምዕራፍ ካላቸው ሁለት መጻሕፍት አንዱ የማቴዎስ ወንጌል ነው፡፡ ማቴዎስ ወንጌሉን የጻፈው ለአይሁድ ስለሆነ የዘር ሐረግን፣ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን በብዛት ይጠቅሳል፡፡ አይሁድ መሢሑን እንዲቀበሉ መሢሑ የአብርሃምና የዳዊት ዘር መሆኑን የሚገልጥ የዘር ፍሰትን ያወሳል፡፡ ለማስረጃም የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን በብዛት ይጠቅሳል፡፡ በዘር ሐረጉ ግን አይሁድ የማይጠቀሙበትን ስልት በመጠቀም አራት ሴቶችን ጠቅሷል (ማቴ. 14 . 5.6.16)፡፡ አይሁድ በዘር ሐረግ ውስጥ ሴቶችን አስገብተው አይቆጥሩም ነበርና፡፡ ክርስቶስ ግን የመምጣቱ አንዱ ዓላማ ይህን ልዩነት ለማስወገድ ነበር፡፡

የማርቆስ ወንጌል- ከወንጌላት ትንሽ ምዕራፎች ያሉት የማርቆስ ወንጌል ነው፡፡ የትምህርቱም ስልት የክርስቶስን የእጁን ተአምራት በመግለጥ በዘመኑ የነበሩ ሮማውያንን ለማሳመን ነው፡፡ ጌታችን በተያዘ ሌሊት እርቃኑን በነጠላ ሸፍኖ ይከተለው ነበርና በያዙት ጊዜ ነጠላውን ትቶ ራቁቱን የሸሸው ወጣት ማርቆስ መሆኑን ብዙ ሊቃውንቶች ይናገራሉ (ማር. 1451-52)፡፡ እናቱ ቤቷን ለአገልግሎት በመልቀቋ የማርቆስ እናት ቤት የመጀመሪያይቱ ቤተ ክርስቲያን የሚል ስያሜ አግኝታለች (ሐዋ. 1212-17)፡፡ ማርቆስ ከበርናባስ፣ ከጳውሎስና ከጴጥሮስ ጋር ብዙ ጊዜ አገልግሏል፡፡ የጴጥሮስም የመንፈስ ልጁ ነው (1ጴጥ. 513) ወንጌሉን የጻፈውም ከእነዚህ ሐዋርያት በጥልቀት በመጠየቅና በማዳመጥ ነው፡፡
የሉቃስ ወንጌል- ሉቃስ ከአሕዛብ ወገን የሆነና በክርስቶስ ያመነ የጳውሎስም ደቀ መዝሙር የሆነ ሰው ነው፡፡ በሙያውም ሐኪም እንደ ነበረ ተጠቅሷል (ቈላ. 414)፡፡ ስለ ክርስቶስም ሙሉ ትረካ ያቀረበ ፀሐፊ ነው፡፡ ወንጌሉን የጻፈው ከአሕዛብ ወገን ለነበረና ላመነ ቴዎፍሎስ ለሚባል ወዳጁ ነው፡፡ ማቴዎስ ወንጌሉን ከዘር ሐረግ ይጀምራል፣ ማርቆስ ከጥምቀቱ ይጀምራል፣ ሉቃስ ግን የኢየሱስ ክርስቶስ መልእክተኛ ከሆነው ከዮሐንስ መጥምቅ የጽንሰት ዜና ይጀምራል፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሉቃስ ወንጌሉንና የሐዋርያት ሥራን ጽፎአል፡፡

የዮሐንስ ወንጌል- ዮሐንስ ወንጌላዊ ከሦስቱ ወንጌላት በተለየ ሁኔታ ወንጌሉን ጽፎአል፡፡ ሦስቱ ወንጌላውያን የኢየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆንና ሰብአዊ ቅርበቱን ተርከዋል፡፡ ዮሐንስ ደግሞ የክርስቶስን መለኮታዊ ክብር በማጉላት ጽፎአል፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰውነትና ፍጹም አምላክነት መቻቻል አለባቸው፡፡ ሰውነቱ አምላክነቱን ጋርዶብን አምልኮ እንዳንነፍገው፣ አምላክነቱ ሰውነቱን ሸፍኖብን እንዳናርቀው መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ የወንጌላውያኑም ጭንቀት ይህ ነው፡፡ ዮሐንስ በአዲስ ኪዳን ውስጥ አንድ ወንጌል፣ ሦስት መልእክታት፣ አንድ የራእይ መጽሐፍ ጽፎአል፡፡




                                      ታሪክ

በአዲስ ኪዳን የታሪክ ክፍል ተብሎ የሚጠራው አንድ ጥራዝ ብቻ ነው፡፡ እርሱም የሐዋርያት ሥራ ነው፡፡

የሐዋርያት ሥራ- የሐዋርያት ሥራን የጻፈው ሉቃስ ነው፡፡ የጻፈውም ወንጌልን ለጻፈለት ቴዎፍሎስ ለተባለው ወዳጁ ነው፡፡ በሉቃስ ወንጌል እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ሲናገር የሐዋርያት ሥራ ደግሞ ከዕርገቱ በኋላ ስላሉት ዐሥር ቀኖችና ስለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ ይናገራል፡፡ የመጽሐፉ ሙሉ ይዘት ወንጌል ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም ከዚያም እስከ መላው ዓለም በእንዴት ያለ ጸጋና ዋጋ መድረሱን የሚተርክ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አድሮ የሠራው ሥራ በመሆኑ የሐዋርያት ሥራ ቢባልም ታሪኩን ስንዘልቀው ግንየመንፈስ ቅዱስ ሥራቢባል መልካም ነበር ያሰኛል፡፡ በዚህ መጽሐፍ በስፋት የተገለጠው የጴጥሮስና የጳውሎስ አገልግሎት ነው፡፡ መጽሐፉ እንደ ሌሎቹ መልእክታት በሰላምታ ወይም በምርቃት አይዘጋም፡፡ ይህ የሚያስረዳን የሐዋርያት ሥራ በትውልድ ሁሉ መቀጠሉን ነው፡፡

                                     መልእክት

የአዲስ ኪዳን ሦስተኛው አከፋፈል መልእክት ነው፡፡ መልእክት የሚባሉት ከሮሜ እስከ ይሁዳ ድረስ ያሉት 21 የመጻሕፍት ጥቅልል ናቸው፡፡ ፀሐፊዎቹም ጳውሎስ፣ ጴጥሮስ፣ ዮሐንስ፣ ያዕቆብና ይሁዳ ናቸው፡፡ የተጻፉትም ለግለሰቦችና ለአብያተ ክርስቲያናት ነው፡፡

የጳውሎስ መልእክታት

ከሮሜ እስከ ዕብራውያን ድረስ ያሉት ዐሥራ አራት መልእክቶች ጳውሎስ የጻፋቸው መልእክቶች ናቸው፡፡ ጳውሎስ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት መካከል አይደለም፡፡ ጌታ ካረገ ከስምንት ዓመት በኋላ ነው የተጠራው፡፡ ክርስትናን በብርቱ ይቃወም በነበረ ሰዓት በደማስቆ መንገድ በመብረቅ ብርሃን ጥሎት፣ ሦስት ቀን ዓይኑን አውሮት በወንጌል አመነ (የሐዋ. 918)፡፡ ከሁሉ ኋላ የተጠራ ቢሆንም ከሐዋርያት ይልቅ ሮጧል፣ ዋጋ ከፍሏል፣ አብያተ ክርስቲያናትን መሥርቷል፣ መልእክታትን ጽፏል፡፡ በመጨረሻም 67 . በሮም አደባባይ በሰይፍ ሞቷል፡፡ መልእክቶቹ ግን ከከዋክብት ደምቀው በዓለም ሁሉ በየዕለቱ ያበራሉ፡፡ መልእክታቱ የተጻፉት ለግለሰቦችና ለአብያተ ክርስቲያናት ሲሆን ምእመናንን ለማጽናት፣ ለመገሰጽ፣ ለማጽናናት፣ ቤተ ክርስቲያንን ፍሬያማ ለማድረግ ባጠቃላይ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመንና በማወቅ ለማደግ ተጽፈዋል፡፡ ጳውሎስ መልእክታቱን የጻፈው ከእስር በፊትና በእስር ዘመን ነው፡፡ መልእክታቱም አብያተ ክርስቲያናቱ በሚገኙበት አገርና ግለሰቦች ተሰይመዋል፡፡ ለምሳሌ፡- የሮሜ መልእክት ሮም ለምትገኘው ቤተ ክርስቲያን የተጻፈ ሲሆን የጢሞቴዎስ መልእክት ደግሞ የጳውሎስ የመንፈስ ልጅ ለሆነው ለኤፌሶኑ ጳጳስ ለጢሞቴዎስ የተጻፈ ነው፡፡

የጴጥሮስ መልእክታት

ጴጥሮስ ከኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት አንዱና የመጀመሪያው ሲሆን የኢየሱስ ክርስቶስን የእጁን ተአምራት፣ የቃሉን ትምህርት በቀጥታ የተቀበለ ነው፡፡ ጳውሎስ የአሕዛብ ሐዋርያ ሲሆን ጴጥሮስ የአይሁድ ሐዋርያ ነበር፡፡ 67 . በሮም አደባባይ የቊልቊሊት ተሰቅሎ እስኪሞት በብዙ ስደትና መከራ ወንጌልን ሰብኮአል፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ሁለት መልእክታትን ጽፎአል፡፡ የመጀመሪያው መልእክቱ በተለያዩ የእስያ አውራጃዎች ስለ ወንጌል ለተሰደዱ ክርስቲያን አይሁዶች የጻፈው ሲሆን በመታገሥ ያለውን ሰማያዊ ዋጋ በመግለጥ ሊያጸናቸው ጽፏል፡፡ ሁለተኛይቱ የጴጥሮስ መልእክት ደግሞ በክርስቲያኖች መካከል ሰርገው ስለገቡ የሐሰት መምህራን (መናፍቃን) ምእመናን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጽፎአል፡፡ ለቤተ ክርስቲያን የአረማውያን ነገሥታትን ያህል የሐሰት መምህራንም ጎጂዎቿ ናቸውና፡፡

የዮሐንስ መልእክታት

ዮሐንስ የክርስቶስን መለኮታዊ ክብር ለማጉላት ወንጌሉን እንደ ጻፈ  ዓይተናል፡፡ ደግሞም ሦስት መልእክታትንም አዘጋጅቷል፡፡ መልእክታቱንም ሆነ ወንጌሉን እንዲሁም ራእዩን የጻፈው በዕድሜው መጨረሻ አካባቢ ነው፡፡ የመጀመሪያይቱን መልእክቱን የጻፈው በዘመኑ ተስፋፍቶ የነበረውን የመናፍቃንን እንቅስቃሴ ለመጋፈጥና ምእመናን በፍቅር እየተባበሩ እምነታቸውን እንዲጠብቁ ለማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛይቱን መልእክት ደግሞ የጻፈው ለአንዲት አማኝ ሴት ሲሆን ከስህተት ትምህርት እንድትጠበቅ ነው፡፡ ሦስተኛይቱ የዮሐንስ መልእክት በቤቱ እንግዶችን ለሚቀበል ጋይዮስ ለተባለ በጎ አማኝ ለምስጋና የጻፈለት መልእክት ነው፡፡

የያዕቆብ መልእክት

ያዕቆብ ከጌታ ደቀ መዛሙርት አንዱ ነው፡፡ ይህ ያዕቆብ ይህችን ቀደምት መልእክቱን የጻፈው በስደት ለተበተኑት ክርስቲያን አይሁድ ሲሆን የመልእክቱ ዋና ዓላማ በመከራቸው እንዲፀኑና እምነታቸውን በምግባር እንዲገልጡ ለማነቃቃት ነው፡፡

የይሁዳ መልእክት

ባለ አንድ ምዕራፍ ከሆኑት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት አንዱ የይሁዳ መልእክት ሲሆን ይሁዳም መልእክቱን የጻፈው በስም ላልተጠቀሱ አማንያን ነው፡፡ የመልእክቱም ዓላማ ክርስቲያኖች ሁሉ እምነታቸውን እንዲጠብቁ ለማስጠንቀቅ ነው፡፡

                                          ትንቢት

በአዲስ ኪዳን ውስጥ የትንቢት መጽሐፍ ተብሎ የሚጠራው የዮሐንስ ራእይ ነው፡፡

የዮሐንስ ራእይ- ዮሐንስ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ተግዞ /ታስሮ/ ሳለ በራእይ ያለፈውን፣ ያለውንና የሚመጣውን ተገልጾለት ጽፏል፡፡ የዮሐንስ ራእይ ክርስቲያኖችን ለማይቀረው የክርስቶስ ምጽአት ያዘጋጃል፡፡ አገላለጹም ሥዕላዊ ነው፡፡ ይህ የሆነው ሥዕል ከብዙ ቃላት ይልቅ የመናገር አቅም ስላለውና ዳግመኛም መጽሐፉን ከአደጋ ለመከላከል ነው፡፡ ትንቢቶቹ በግልጽ ቢጻፉ ኖሮ አረማውያን ነገሥታት በቶሎ ይጠፉታልና ጠላት ለመቀነስ ነው፡፡

ይህንን ጥናት ስናጠና የመጽሐፍ ቅዱሳችንን ማውጫ እየተመለከትን ብናጠና ይበልጥ ይብራራልናል፡፡ አንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በምዕራፍ ይከፈላል፡፡ ምዕራፉ ደግሞ በቊጥር ይከፈላል፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሲጠቀስ በአጭሩ ይጠቀሳል፡፡ ለምሳሌ፡- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ አሥራ አምስት ቊጥር ስድስት ቀጥሎ ባለው መልኩ ይጠቀሳል፡- (ዘፍ. 15 6)፡፡