Thursday, April 7, 2016

❖ዘንዶውን በኒውክሌር እናግዛለን፤አምላክንም እናሸንፋለን

‹‹ዘንዶውን በኒውክሌር እናግዛለን፤አምላክንም እናሸንፋለን!››

የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ
ሁሉም ኢትዮጵያዊ አቅልሎ ያየው፤ነገር ግን እጅግ ከባድና ትኩረት ልንሰጠው የሚገባን ነጥብ ነበር፡፡
ኢትዮጵያን አቅልለንና ንቀን የምናያት እኛ ዜጓቿ ብቻ ነን፡፡በአሁኑ ሰዓት ግን ይህ ራስን የመናቅ አባዜ ማክተም ያለበት ይመስላል፡፡
ወደደድንም ጠላንም፣አመንንም አላመንንም፣አማኝም ሆንን ኢኣማኒ ይቺ ዓለም መጥፋቷ አይቀርም፡፡መጥፊያዋ ደግሞ ተቃርቧል፡፡
በትንቢቱም ይሁን በሳይንስ፤አሊያም በአየር ብክለት ወይም በሌላ የተፈጥሮ አደጋ ዓለም ልትጠፋ ብትችል የሰውን ልጅ ላያሳስበው ይችላል፡፡
ይህን የዓለም ጥፋት ጉዳይ ወደ ኢትዮጵያ ስናመጣው ግን መልኩን ይቀይራል፡፡
ኢትዮጵያ የዓለም መነሻ ነበረች፤አሁንም የዓለም መጨረሻና መደምደሚያ መሆኗ ገሀድ እየሆነ ነው፡፡ይህንን እኛ ኢትዮጵያውያውያን አናምንም፤አንቀበልም፡፡ሌላው ዓለም ግን አምኗል ተቀብሏል፡፡
በቅርቡ ማለትም በኛ አቆጣጠር በ 2007 ዓ.ም አጋማሽ ፍስሐ ያዜ ካሳ በተባለ ጋዜጠኛና ደራሲ የተፃፈ መፅሀፍ ነበር፡፡ርዕሱ ‹‹የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ›› ይሰኛል፡፡ይህ መፅሐፍ ምንም እንኳን ለደራሲው መጥፊያው ቢሆንም አገኘሁ ያለውን እውነት ለኢትዮጵያውያን ሊያሳይበት ሞክሯል፡፡
የዚህ መፅሐፍ ትኩረት ስለ አዲሱ የምድር መንግስት ምስረታ ብቻ አይደለም፡፡የፍፃሜው ጦርነት ምን እንደሚመስል፣ኢትዮጵያም ከፍፃሜው ጦርነት ጋት በተያያዘ የተለየ ትኩረት እንደተደረገባት፣‹‹ዘንዶውን በኒውክሌር እናግዛለን፤እግዚአብሔርንና መላዕክቱንም እናሸንፋለን›› ብለው የኃያላን አገራት መሪዎችና የቫቲካን ቤተክርስቲያን የሚዝቱበትና የሚዘጋጁበት፤ ጦርነቱም በዋናነት ኢትዮጵያ ላይ እንደሚሆን፤ጎላቸውም ኢትዮጵያ እንደሆነች ይገልፃል፡፡የዓለማችን ታላላቅ የሚባሉ አገራትና መሪዎች ከዚህ በኋላ ትልቁ የቤት ስራቸው ኢትዮጵያ ላይ እንደሆነ በማስረጃ እያስደገፈ ተንትኖታል፡፡
ይህ መፅሀፍ በአሁኑ ጊዜ በብዙሃኑ ዘንድ እየተነበበ ያለ ቢሆንም፤በጥቂቶች ዘንድ እንደ ልብ ወለድ እየተቆጠረ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ነገር ግን ይህ መፅሀፍ ከተፃፈ በኋላና ለህትመት በቅቶ ወደ አንባቢው መድረስ በጀመረ ማግስት የተፃፉት ነገሮች አንድ ባንድ እየተተገበሩ መጡ፡፡
ፀሐፊው የ G 20 አገራትና የ G 8 አገራት መሪዎች ስብሰባ በሙሉ ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዘ መሆኑን እየገለፀ ቃል በቃል የዝግ ጉባዔያቸውን ጭብጥ እንደወረደ አስፍሮታል፡፡በፍስሐ አባባል መረጃው የወጣው ከኋይት ሀውስ ነው፡፡
በዋናነት የሚፈልጉት የጣና ሐይቅን አካባቢ ቢሆንም ሙሉ ኢትዮጵያ ዋና ጎላቸው ናት፡፡በዚህ መሰረት የጣና ሐይቅ ምንነቱ ባልታወቀ እንግዳ አረም ከመሸፈን ጀምሮ እስከ አቡነ ማቲያስ ወደ ቫቲካን መጓዝ ድረስ በርካታ ነገሮችን መዘርዘር ይቻላል፡፡ሆኖም ነገሩን ለማሳጠርና በመፅሐፉ የተባሉት ነገሮች ፈጥነው እየተተገበሩ እንዳሉ ለማሳየት የተወሰኑትን ብቻ ልጥቀስ፡፡
መፅሐፉ በ2007 ዓ.ም ለህትመት በበቃ ማግስት ለምሳሌ፤
1. የዓለማችን ቢሊየነር ቢልጌትስ/የስሙ ትርጉም 666 ነው/በቫቲካኑ ጳጳስ እና በአሜሪካ መንግስት አዛዥነት ረቀቅ ባለ ዘዴ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ እንደሚወዳጅና የክብር ዶክትሬት እንደሚሰጡት ያትታል፡፡ወዲያውም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ዶክትሬቱን ወሰደ፡፡ብዙ የሰራላት አገሩ አሜሪካ እንኳ ያልሰጠችውን ዶክትሬት እኛ ሰጠነው፡፡ይህ ሊሆን የቻለው ቢልጌትስ ወደ ፊት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በኢትዮጵያ በመመደብ ኢትዮጵያዊ ህፃናትንና ሌሎችን በተለይም በገጠራማው ክፍል ያሉትን ማህበረሰቦች የአስተሳሰብ አድማሳቸውን ለማስፋት በሚልና በልማት ስም/በትምህርት፣በጤና፣ በውሃ፣…ወዘተ/በሚል መድሃኒት እየሰጡ ቀስ በቀስ አስተሳሰባቸውን ለማጥፋት እንዲመች ሲባል ለተነደፈው ዕቅድ ነው፡፡
2. ሁሉም የኃላን አገራት መሪዎች/የ666 ዓባላት/በጳጳሱ በአቡነ ፍራንሲስ አዛዥነት ወደ ኢትዮጵያ መሄድ እንዳለባቸውና የባፎሚትን፤በፍስሀ አገላለፅ የዘንዶውን፣በመፅሐፍ ቅዱስ አገላለፅ የአውሬውን፣በተከታዮቹ አገላለፅ የሉሱፌልን፣በጥቅሉ የሳጥናኤልን ዓላማ ለማሳካትና ኢትዮጵያ ላይ ለሚኖረው መንፈሳዊ የፍፃሜ ጦርነት ዝግጅት ሲባል እንዲያጠምቁዋቸው መታዘዛቸውን አንብበን ነበር፡፡ይህን በፍስሐ መፅሀፍ ባነበብን ማግስት ደግሞ ባራክ ኦባማ ወደ ኢትዮጵያና ወደ ሌላው የምስራቅ አፍሪካ አገራት መጣ፡፡መጥቶም ስለ ወንድ ለወንድ ጋብቻ ነፃነትና ስለሌላው ነገር ደስኩሮ ሄደ፡፡
3. ከቆይታ በኋላ ደግሞ ታስቦም ታልሞም በማያውቅ መንገድ በቀጥታ ከዘንዶው መልዕክት ተቀብለው ለኃያላን አገራት መሪዎችና ለዓለም የሐይማኖት አባቶች ትዕዛዝ የሚያስተላልፉት ራሳቸው አቡነ ፍራንሲስ ወደ ኬንያና ውጋንዳ፣ቀጥሎ ወደ መካከለኛው አፍሪካ መጡ፡፡ቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ ቢመጡ ከፍተኛ ቁጣ እንደሚነሳባቸው ስለሚውቁ ወደ ጎረቤት አገር ሄደው የተንኮል ችግኛቸውን ተክለው ተመለሱ፡፡እንደተመለሱ ደግሞ የኛውን ጳጳስ አቡነ ማቲያስን ወደ ቫቲካን አስጠርተው አነጋገሩ፡፡የግብፁ አቡንም ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውና በመስቀል አደባባይ ንግግር ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
4.በተመሳሳይ ሁኔታና ለተመሳሳይ አጀንዳም የቀድሞው የአሜሪካ መሪ ቡሽ በድብቅ መጥቶ ላሊበላንና ሌሎችን ቦታዎች ጎብኝቶ ሾልኮ ሊሄድ ሲል ሚስጥሩ ወጣና ይፋዊ ዜና ሆነ፡፡ተደብቆ መምጣቱ ለምን እንዳስፈለገም አልታወቀምና ብዙዎችን ግራ አጋባ፡፡
5.የቻይና፣የጃፓን፣የቱርክና የሌሎች የG20 አባል አገራት በተካካይ ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውና፤ለህንድና ለሌሎች አገራት የብሄር ግጭትን የፈጠሩ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶች መሰጠት፣የጃፓን ግዙፍ የንግድና የገንዘብ ተቁዋም መመስረት፣በመቶ ኪሎ ሜትር ካሬ የሚገመት ቦታ ለጅቡቲ ውሃ ማውጫ በሚል ከኢትዮጵያ መሬት ላይ ተቆርሶ ለ 30 ዓመት ለጅቡቲ መሸጡ፣ሶቨሪ ቦንድ በፓርላማ ጸድቆ ተግባራዊ መሆኑና ወዘተ..የተባሉት ነገሮች ወደ ተግባር ፈጥነው እየተለወጡ ለመሆናቸው አመላካች ነው።
6. በቅርቡ ደግሞ በመፅሃፉ እንደተገለፀው የኢጣሊያው መሪ ባልተለመደ ሁኔታ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ረጅም በሚባል መልኩ 5 ቀናትን አሳለፈ፤ላሊበላንም ሌላውንም ጎበኘ…፡፡
(በነገራችን ላይ እነዚህን ገጠመኞችና መምጣት መሄዶችን እንደ ተራ ክስተተት ወይም ገጠመኝ የማናይበት ምክንያት በመፅሐፉ ውስጥ በተገለፀው መሰረትና በፕሮግራማቸው መሰረት የተከናወኑ በመሆናቸው ነው፡፡
የእያንዳንዱ አገር መሪ ጎላቸው ኢትዮጵያ እንደሆነች የተገለፀላቸው በ 2014ቱ የ G 20 ስብሰባ ላይ ነው፡፡በጳጳሱ በአቡነ ፍራንሲስ ሰብሳቢነት ሲነጋገሩባትና በዝግ ስብሰባቸው ላይ ስለ ኢትዮጵያ ሲያነሱ፤መሪዎቹ እየተገረሙና እየተደነቁ ያነሱዋቸውን ጥያቄዎችና መልሶች መፅሐፉ ውስጥ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡በፍጥነትና በተከታታይ ወደ ኢትዮጵያ መሄድ እንዳለባቸውም የታዘዙት በዚሁ ጉባኤ ላይ ነው፡፡)
7.ቀጥሎ ደግሞ በመፅሐፉ በተገለፀው መሰረት ከሳምንታት በፊት የኢትዮጵያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ማቲያስ ወደ ሮም ተጓዙ፡፡ተጉዘው ሽልማትም ተሰጥቶዋቸው መጡ፡፡ዝቅ ብላችሁ ምስሉን እንደምታዩት ከ አቡነ ፍራንሲስ ጋር ተሳስመው፣ተነጋግረው በኢትዮጵያውያን ምዕመንም ተሳልቀው መጡ!
8.ታስታውሱ እንደሆነ በሚሊኒየማችን ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ወጣት ኢትዮጵያዊ ለማጥመድ ትጠቅማለች ተብላ የተላከችው ቢዮንሴ የተባለችው ዘፋኝ(አሁን አምላክ ሆና፤የራሱዋን ቤተ ክርስቲያን መስርታ፤የራሱዋን መፅሐፍ ቅዱስ አፅፋ እየተመለከች ነው)መጥታ በአደባባይ የኢትዮጵያን ህፃናት ሰብስባ ባፎሚትን አስመልካ እንደሄደችው ሁሉ፤አሁንም ሰፊውን የኢትዮጵያ ወጣት ክፍል ለማጥመድ ሌላ ዘዴ ተፈለገ፡፡ ኢትዮጵያውያውያን ወጣቶች የተወሰዱበት ኳስ ሆኖ ስለተገኘም እነሱን ለማጥመድ በኳስ ዙሪያ ኢትዮጵያ ላይ መሰረት ተጣለ፡፡የዚህ ከፍተኛ ኃላፊነትም በፊፋ ላይ ወደቀ፡፡ስለዚህ በሴፍ ብላተር የተተኩት አዲሱ የፊፋው ፕሬዘዳንት በተመረጡ ማግስት የመጀመሪያ ስራቸው ያደረጉት ወደ ኢትዮጵያ መምጣትና መጎብኘት ነበር፡፡ከሶስት ቀናት በፊት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ጎብኝተው ሄዱ፡፡ኢትዮጵያ ታሪካዊ አገር ስለሆነች መጎብኘት ፈልገው አይደለም፡፡ያ ቢሆን ከመመረጣቸው በፊት ሰፊ ጊዜ ነበራቸው፡፡ወይም ከተመረጡ በኋላ ሌሎች ስራዎቻቸውን አስቀድመው ተረጋግተው መጎብኘት ይችሉ ነበር፡፡የመምጣታቸው ዓላማ ሌላ ስለሆነ ግን በኳስ መቃብር አገር በኢትዮጵያ ፈጥነው ተገኙ፡፡
9.ይህ ከመሆኑ ከጥቂት ጊዜ በፊት ደግሞ ሴፍ ብላተር በወረዱ ማግስት አዝናኝና ዲፕሎማሲያዊ አቀራረብ ባለው መንገድ ለስለስ ተደርጎ አንድ ዜና ተነገረን፡፡ዳሽን ቢራ ምንም በማይገናኝና በማይመስል መንገድ ከአርሰናል ጋር የረጅም ዓመት የምናምን ውል አደረጉ፡፡…ወዘተ…ተብሎ በበጎ ጎኑ የታየ ዜና ተነገረን፡፡እንዴት ኢትዮጵያን?እያለ የሚጠይቅ ካለ ምላሹን በቀላሉ ማግኘት ይችላል፡፡
10.ከጥቂት ሳምንታት በፊት ደግሞ ዓለምን በአንድ በአውሬው /በ666/ አገዛዝ ስር ለማስገዛት የሚታትሩት የሃያላን አገራት መሪዎችና የቫቲካን ቤተክርስቲያን እንቅፋት የሆነችባቸው ብቸኛ አገር ሶሻሊስቷ ኩባ ነበረችና ባልተለመደ ሁኔታ በመጀመሪያ ጳጳሱ ፍራንሲስ ወደ ኩባ ተጉዘው ኩባን ጎበኙ፡፡ቀጥሎ ደግሞ ዓለምን ባስገረመ መንገድ ኦባማ ራሱ ወደ ኩባ ሄዶ ለማሳመን ሞከረ፡፡ከሽብርተኝነት ሊስት አውጥተናችኋል አሏቸው፡፡ለ90 ዓመታት አደገኛ ጠላት ሆነው የቆዩ ነበሩ፡፡ባሁኑ ሰዓት የ 666 ማይክሮ ችፕ (የአውሬው ምልክት)በአገሬ ህዝብ ላይ አይገጠምበትም ብሎ የሚዝተው ብቸኛው ሰው አዛውንቱ ፊደል ካስትሮ ብቻ ነው፡፡ቢሆንም የአገሪቱ ፕሬዘዳንት የፊደል ካስትሮ ወንድም ራውል ካስትሮ ለዘብ ሊልላቸው ሞክሮዋል፡፡ሁለቱ ባይስማሙ እንኳን እድሜያቸው ስለገፋና በቅርቡ መሞታቸው ስለማይቀር፤ዋናው ህዝቡን ማሳመን ነውና ጳጳሱ በኩባ ጉብኝታቸው ከፍተኛውን የካቶሊክ እምነት ተከታይ ቀልብ መግዛት ችለው ነው የተመለሱት፡፡
ይህ ሁሉ ነገር በገጠመኝ እንዳልሆነ ብቻ ሳይሆን፤ለምን እንደሚሆንና መቸ እንደሚሆን ቀድሞ የነገረን ፍስሐ ያዜ ነው፡፡በዚህ ድንቅ መፅሐፍ ውስጥ የአቡነ ፍራንሲስና የኃያላን አገራት መሪዎች ሴራ በደንብ ተተንትኗል፡፡የዘመኑ ስሌትና ቀመርም እንዲሁ፡፡ይህ ሁሉ ውጣ ውረድ ዓለምንና ህዝቦቿን በረቂቅ ቴክኖለጂ አጋዥነት ጠቅልሎ በአንድ በሳጥናኤል አገዛዝ ስር ለማድረግ ሲባል ነው፡፡ለዚህም ሁሉም በየፊናው ተሰማርቶ ይገኛል፡፡የአገር መሪ፣የሐይማኖት መሪ፣የሙዚቃው ኢንደስትሪ መሪ…ከፍተኛ የገንዘብ አቅምና በቢሊዮን የሚቆጠር ተከታይ ያለው የእንግሊዝ ኳስ፣ወዘተ…!የሁሉም ትኩረት ደግሞ ኢትዮጵያ!ናት፡፡
ለምሳሌ ቢዮንሴ የተባለችው ዘፋኝ በሚሊኒየማችን ወቅት መጥታ በአቡነ ጳውሎስ አማካኝነትና መልካም ፈቃድ ወደ ቤተ መቅደሳችን ገብታለች፡፡ያውም ከነጫማዋ፡፡ ስትጨፍር አድራ በሚኒስከርትና በሂል ጫማ ሆና፤በከበሮ፣በፀናፅልና በወርቅ ጥላ ታጅባ ነው በቤተ መቅደስ አቀባበል የተደረገላት፡፡በዚያ ወቅት በእርዳታ ልብስ ጀቡና የባፎሚትን ፅላት ተክላ መሄዷ እንዳለ ሆኖ፤አሁን ደግሞ the national church of bey በሚል ቤተክርስቲያን መስርታ አምላክ ሆና እየተመለከች ነው፡፡bible የሚለውንም beyble በሚል ቀይራ የራሱዋን ባይብል እያሳተመች ነው፡፡ዝቅ ስትሉ ምስሉ ላይ እንደምታዩት ቢዮንሴ እግዚአብሔርን ተክታ እየተመለከች ነው፡፡
ዓለም ይህን ሁሉ ነገር እያነሳ ሲጥል የኛው ድንቅ ደራሲ ግን ቀድሞ ሁሉንም ነገር ነግሮን ነበር፡፡ያውም በሚገባን መንገድና በሚገባን ቋንቋ!
ፍስሐ ያዜ ‹‹የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ›› በሚለው መፅሀፉ ከአዳም በፊት ከነበሩት ፍጥረቶች ጀምሮ እስካሁኑ ዘመን ድረስ ምን ምን እንደተከናወነና ያ ሁሉ ክንውንም ኢትዮጵያን ከማጥመድ ጋር የተያያዘ እንደነበር በማስረጃ እያስደገፈ ይነግረናል፡፡ወደ ፊት ምን እንደሚከሰትም እንዲሁ፡፡
የቫቲካኑ ጳጳስ ብዙ ግፍ የፈጸሙ ከመሆናቸውም በላይ በ100ሺ ህፃናት መስዋዕትነት የተከሰሱ ናቸው፡፡ህፃናትን እየሰው ሳጥናኤልን ያገለግላሉ፡፡የቫቲካን ቤተክርስቲያንግብረ ሰዶማውያንን የፈቀደች ናት።ጳጳሱም ቆመው በክብር እያጋቡዋቸው ይገኛሉ።የመጽሀፍ ቅዱሱ ሰድምና ገመራ በነሱ ዘንድ ሀጢያት መሆኑ ቀርቶ እንደ ትልቅ መባረክ ተቆጥሮዋል።በ june 2015 ደግሞ በቫቲካን የሀይማኖት መሪዎችን ሰብስበው አምላክ በሙሴ 10ቱ ትዕዛዛት ላይ 2 ጨንሮልናል በማለት ሁሉም ሰው ማይክሮ ችፑን በጸጋ እንዲቀበልና የጾታ እኩልነት ገደብ ሳይጣልበት የወንድ ለወንድ ጋብቻ የተቀደሰ እንደሆነ በምግለጽ አስጨብጭበዋል።ስበመፅሐፉ ውስጥም ግብረሰዶማዊ ከሆነው ከኦባማ ጋር በስብሰባው መድረክ ላይ ሆነው ሲዳሩ ይታያል፡፡የኦባማ ሚስትም ወንድ መሆኗና ልጆቹም በአንጀሊና ጆሊ አማካኝነት ከኢትዮጵያ በማደጎ የተወሰዱ እንደሆኑ ወዘተ….በመፅሐፉ ይተረካል፡፡
‹‹ነገር ግን…››ይላል ፍስሐ በመፅሃፉ ብዙ ከነገረን በኋላ፤‹‹ነገር ግን….ኢትዮጵያውያን ነጭ አምላኪ ስለሆንን በአማርኛ ስለተፃፈና በኢትዮጵያዊ ፀሀፊ ስለተፃፈ ወይም ነጭ ስላልፃፈው ብቻ ኢትዮጵያውያን አይቀበሉትም!ስለዚህ ይህን መረጃ በሙሉ በነጭ በኩል ማውጣት ብቸኛ አማራጭ ነው!››በማለት በቁጭት ይነግረናል፡፡ለዚህም ይመስላል መፅሐፉ January 2016 ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው፡፡በቅርቡ ይህን የፍስሐ ያዜን መፅሐፍ በአትላንታ የሚገኝ አንድ ክርስቲያናዊ ተቋም ወደ እንግሊዝኛ ተርጉሞ በማሳተም ለንባብ አብቅቶታል፡፡‹‹the goal of satan›› በሚል ርዕስ ነው የተተረጎመው፡፡ምናልባትም ዘ ጎል ኦፍ ሳታን ላይ የቫቲካኑ ጳጳስ ሴራቸውና ጸረ ኢትዮጵያነታቸው ስለተገለፀባቸው ይመስላል በስደተኞች አሳበው አንድ ነገር ፈጥነው አደረጉ፡፡ትሁትነታቸውን ለማሳየት ብለው በአውሮፓ የሚገኙትን ስደተኞች እግር የማጠብ ፕሮግራም ያዙና የኢትዮጵያውያንንና የኤርትራውያንን እግር አጥበው መሳም ጀመሩ፡፡ይህ ተግባራቸውም በዓለም ሚዲያ ተሰራጨላቸው፡፡ምስሉን ዝቅ ብላችሁ መመልከት ትችላላችሁ፡፡
በነገራችን ላይ ቀደም ብሎ የተሰራ አንድ ተከታታይ ፊልም ነበር።አሁን በታዋቂ ቻናሎች እየታየ ነው፡፡የዓረብ ቻናል ተጠቃሚዎች ካላችሁ በቀላሉ አክሽን ላይ መከታተተል ትችላላችሁ፡፡የፊልሙ ርዕስ sleepy hollow ይሰኛል፡፡ይህ ፊልም ከሚያነሳቸው ጭብጦች ውስጥ አንዱ፤በግእዝ ስለተፃፉ ጥንታዊ የኢትዮጵያ መፃህፍት ሲሆን፤ በዋናነት ስለ ‹‹መርበብተ ሰለሞን››ይተርካል፡፡መርበብተ ሰለሞን ደግሞ ከግዕዝ ወደ ሁሉም የዓለም ቋንቋዎች ተተርጉሞ በሚስጥራዊ አባላት ዘንድ በደንብ የተፈተሸና አስፈላጊነቱ የታመነበት መፅሐፍ ነው፡፡እኛ ደግሞ በግእዝ ስለተፃፈ ብቻ ሚስጥሩ ሳይገባንና ንቀነው ሁሉንም ሰነድ ተረት ተረት ብለነዋል፡፡ የሚገርመው ግን በፍስሐ መፅሐፍ ውስጥ ሁሉም የኃያላን አገራት መሪዎችና የቫቲካኑ ጳጳስ ግእዝ ተናጋሪዎች እንደሆኑና፤ከዘንዶው በተሰጣቸው ጥበብ ተጠቅመው በግእዝ ለልዑላቸው ለሳጥናኤል ቅኔ እንደሚዘርፉ፤አጠቃላይ የውጊያቸው ቀመር የግእዙን ሰነድ ተንተርሶ እንደሆነ በደንብ ይብራራል፡፡ስለ መፅሐፈ ሄኖክም ብዙ የሚለው አለ፡፡
ስለ ፍስሐ ያዜ መፅሀፍ በዚህ አጭር ገፅ አውርቶ መጨረስ አይቻልም፡፡ ብቻ ግን ‹‹የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ›› የሚለውን መፅሐፍ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንዲያነበው መጠቆም እፈልጋለሁ፡፡ይህን ፅሁፍም ለቁም ነገረኛ አንባቢያን ሼር እንድታደርጉት እመክራለሁ፡፡ቢያንስ ቢያንስ በዙሪያችን ምን እየተከናወነ እንዳለ ባናውቅ እንኳን ምን እያንዣበበብን እንዳለ ማወቁ ጠቃሚ እንጂ ጎጅ ነገር የለበትም፡፡
አንድ ነገር ልጨምር፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊት የቫቲካኑ ጳጳስ አቡነ ፍራንሲስና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ማቲያስ ወዳጅነታቸውን በዓለም ፊት አውጀዋል፡፡የቫቲካን ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የኢትዮጵያን ውድቀት የሚሹ ከመሆናቸውም በላይ፤በቀጥታና በተዛዋሪ በአገሪቱና በሐይማኖተኛው ላይ ከፍተኛ ጥፋት ፈፅመዋል፡፡ጨርሶ ወዳጅነት የሚባል ነገርም የለም!በሞሶሎኒ ዘመን እንኳ የኢጣሊያን ታንክ ባርከው፣ሰራዊቱን መርቀው ‹‹ኢትዮጵያን ውረሩ፤ሰውንም አገሩንም በመርዝ ጋዝ አጥፉ!››ብለው ከመሸኘታቸውም በላይ፤የቤተክርስቲያኒቱን የወርቅ መስቀል ለጦርነቱ እንዲያውሉት በስጦታ ሰጥተዋል፡፡ከዚያ ዘመን ጀምሮም የቫቲካን ቤተክርስቲያንና ጳጳሳቱ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያንና ህዝቡን፤እንዲሁም ኢትዮጵያን ይቅርታ እንዲጠይቁ ብዙ ጊዜ በሐይማኖት አባቶችና በምሁራን ተለምነው አሻፈረን ያሉ ናቸው፡፡ዛሬ ግን ከኋላ የመጣ ዓይን አወጣ እንዲሉ አቡነ ማቲያስ ወደ ቫቲካን ተጉዘው፤የዶለቱትን ዶልተው፤ሽልማታቸውንም ተቀብለው፤እንዲህ ሲሉ ተናገሩ፤‹‹ከቫቲካን ጋር ፍቅር ነበርን፡፡የነበረንን የቀድሞ ፍቅር እንመልሰዋለን!››በማለት ተሳለቁ፡፡ የአቡነ ማቲያስ ወደ ቫቲካን መሄድ ለበርካታ ኢትዮጵያውያውያን እንግዳ ነገር ሆኖዋል፡፡ይህ ጉዳይ እንቆቅልሽ የሆነበት ካለ፤‹‹የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ›› የሚለውን መፅሐፍ ሲያነብ እንቆቅልሹ ይፈታለታል ባይ ነኝ፡፡.
                   አምላክ ኢትዮጵያን ይባርክ፡፡

No comments:

Post a Comment