❖ መጻጉዕ፦
( ፈዋሻችን ኢየሱስ ክርስቶስ)
መጻጉዕ የዐቢይ ጾም 4ኛ ሳምንት ነው፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተገለጠበት ዘመን የፈወሳቸውን ሕሙማን ማስረጃ በማድረግ ከፈወሳቸው ሕሙማን፥ ካነጻቸው ለምጻሞች፥ ቀን ካወጣላቸው ሰዎች፥ ከሰው ከቀላቀላቸው ግፉአን፥ ጋር በመቆም ቤዛችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የምናመሰግንበት ሳምንት ነው፡፡ ለአምልኮ የተመረጠው የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 5 ነው፡፡በወንጌሉ እንደተጻፈው ባለታሪኩ ሰውነቱ የሰለለ፤ ወደ መጠመቂያይቱ ተጋፍቶ የሚያስገባው ሰው የሌለው፤ ለብዙ ዘመናት ፈውሱን በተስፋ ሲጠብቅ የነበረ ሰው ነው፡፡ፈዋሹ ጌታ ኢየሱስ "ልትድን ትወዳለህን ? " ብሎ ጠየቀው፡፡እርሱም "ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት።" ኢየሱስ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው።ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ። ዮሐ 5:7-12:: ክብር ለፈዋሹ!!
➊ ፈዋሽ እግዚአብሔር ነው፡፡ ሰዎች በተለያዩ ደዌዎች ሊያዙ ይችላሉ፤ ፈዋሹ ግን ሁሉን በሁሉ የሚሠራ እግዚአብሔር ነው፡፡ ፈዋሹ በነፃ የሚፈውስ፥ ጤናን የሚመልስ አምላክ ነው"እኔ ጤናህን እመልስልሃለሁ ቁስልህንም እፈውሳለሁ" ኤር 30:17፡፡ በአንድም በሌላም በብዙም በጥቂትም ያድናል፡፡እኔ ፈዋሽህ ነኝ ያለ ቁስላችንን የማይፀየፍ አምላክ ነው፡፡ፈዋሹን የጠበቀ አንድ ቀን አልጋውን ተሸክሞ መሄዱ አይቀርም፡፡በዘመናችን ከእግር ጥፍራ እስከ ራስ ፀጉር ደዌ በሁሉ ሆኗል ፣ራስ ሁሉ ለህመም ልብም ለድካም ሆኗል ስሙን እየቀያየረ ደዌ ይመጣል፤ የስጋት ምንጭም ሆኗል፤ መፍትሔው ፈዋሹ ነው። ኢየሱስ ዛሬም በስሙ፣ በቃሉ እና በመንፈሱ ይፈውሳል። "እኔ ፈዋሽህ እግዚአብሔር ነኝ" ዘጸ 15:26
➋ድኅነት የሰውን ፈቃድ ይፈልጋል፡፡ ፈውስ፣ ስጦታ እና ድኅነት የእግዚአብሔር የቸርነት ብልጽግና ፍሬዎች ናቸው፡፡እግዚአብሔር ለጥቅማችን የሆነን ነገር እንኳ አስፈቅዶ ያደርጋል፡፡ልትድን ትወዳለህ ብሎ ጠይቆ ነውና ያዳነው፡፡ጌታ ሲፈውስ ያለ ፈቃድ የፈወሳቸው በአጋንንት እስራት የተያዙትን ብቻ ነው፤ ይህን ያደረገው አእምሯቸው በሌላ አዛዥ ስለተያዘ ተናጋሪው ተከራዩ እንጂ ሕመምተኛው ስላልሆነ ነው፡፡እኛም የተያዝንበት ሕመም፥ ፈውስ ፍለጋ የወጣንበት ቁስል ይኖረናል። ፈዋሹ እግዚአብሔር ሊፈውሰን ፈቃዱ ነው፤ ምሕረቱ ግን ለሮጠ ወይም ለቀደመ ሳይሆን በእምነት ፈቃድ ለተከተለ ነው፡፡"እንግዲህ ምሕረት ለወደደ ወይም ለሮጠ አይደለም፥ ከሚምር ከእግዚአብሔር ነው እንጂ።"ሮሜ 9:16። በደዌ ሥጋ ወነፍስ ለተያዝን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ፈውስ ይሁን!!!
( ፈዋሻችን ኢየሱስ ክርስቶስ)
መጻጉዕ የዐቢይ ጾም 4ኛ ሳምንት ነው፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተገለጠበት ዘመን የፈወሳቸውን ሕሙማን ማስረጃ በማድረግ ከፈወሳቸው ሕሙማን፥ ካነጻቸው ለምጻሞች፥ ቀን ካወጣላቸው ሰዎች፥ ከሰው ከቀላቀላቸው ግፉአን፥ ጋር በመቆም ቤዛችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የምናመሰግንበት ሳምንት ነው፡፡ ለአምልኮ የተመረጠው የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 5 ነው፡፡በወንጌሉ እንደተጻፈው ባለታሪኩ ሰውነቱ የሰለለ፤ ወደ መጠመቂያይቱ ተጋፍቶ የሚያስገባው ሰው የሌለው፤ ለብዙ ዘመናት ፈውሱን በተስፋ ሲጠብቅ የነበረ ሰው ነው፡፡ፈዋሹ ጌታ ኢየሱስ "ልትድን ትወዳለህን ? " ብሎ ጠየቀው፡፡እርሱም "ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት።" ኢየሱስ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው።ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ። ዮሐ 5:7-12:: ክብር ለፈዋሹ!!
➊ ፈዋሽ እግዚአብሔር ነው፡፡ ሰዎች በተለያዩ ደዌዎች ሊያዙ ይችላሉ፤ ፈዋሹ ግን ሁሉን በሁሉ የሚሠራ እግዚአብሔር ነው፡፡ ፈዋሹ በነፃ የሚፈውስ፥ ጤናን የሚመልስ አምላክ ነው"እኔ ጤናህን እመልስልሃለሁ ቁስልህንም እፈውሳለሁ" ኤር 30:17፡፡ በአንድም በሌላም በብዙም በጥቂትም ያድናል፡፡እኔ ፈዋሽህ ነኝ ያለ ቁስላችንን የማይፀየፍ አምላክ ነው፡፡ፈዋሹን የጠበቀ አንድ ቀን አልጋውን ተሸክሞ መሄዱ አይቀርም፡፡በዘመናችን ከእግር ጥፍራ እስከ ራስ ፀጉር ደዌ በሁሉ ሆኗል ፣ራስ ሁሉ ለህመም ልብም ለድካም ሆኗል ስሙን እየቀያየረ ደዌ ይመጣል፤ የስጋት ምንጭም ሆኗል፤ መፍትሔው ፈዋሹ ነው። ኢየሱስ ዛሬም በስሙ፣ በቃሉ እና በመንፈሱ ይፈውሳል። "እኔ ፈዋሽህ እግዚአብሔር ነኝ" ዘጸ 15:26
➋ድኅነት የሰውን ፈቃድ ይፈልጋል፡፡ ፈውስ፣ ስጦታ እና ድኅነት የእግዚአብሔር የቸርነት ብልጽግና ፍሬዎች ናቸው፡፡እግዚአብሔር ለጥቅማችን የሆነን ነገር እንኳ አስፈቅዶ ያደርጋል፡፡ልትድን ትወዳለህ ብሎ ጠይቆ ነውና ያዳነው፡፡ጌታ ሲፈውስ ያለ ፈቃድ የፈወሳቸው በአጋንንት እስራት የተያዙትን ብቻ ነው፤ ይህን ያደረገው አእምሯቸው በሌላ አዛዥ ስለተያዘ ተናጋሪው ተከራዩ እንጂ ሕመምተኛው ስላልሆነ ነው፡፡እኛም የተያዝንበት ሕመም፥ ፈውስ ፍለጋ የወጣንበት ቁስል ይኖረናል። ፈዋሹ እግዚአብሔር ሊፈውሰን ፈቃዱ ነው፤ ምሕረቱ ግን ለሮጠ ወይም ለቀደመ ሳይሆን በእምነት ፈቃድ ለተከተለ ነው፡፡"እንግዲህ ምሕረት ለወደደ ወይም ለሮጠ አይደለም፥ ከሚምር ከእግዚአብሔር ነው እንጂ።"ሮሜ 9:16። በደዌ ሥጋ ወነፍስ ለተያዝን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ፈውስ ይሁን!!!
No comments:
Post a Comment