Wednesday, May 27, 2020

❖አርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፤ ወነበረ በየማነ አቡሁ፦

አርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፤ ወነበረ በየማነ አቡሁ፦
       (ጸሎተ ሃይማኖት አንቀጽ 7)

    ዓለምን በሞቱ ና በትንሳኤው በፍቅሩና በኀይሉ ማርኮ ዐረገ። 

ስለዚህ፦ ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ምርኮን ማረከ ለሰዎችም ስጦታን ሰጠ ይላል።
ሰይጣንን የማረከው በሃያልነቱ ነው።
ከእርሱ ይልቅ የሚበረታ መጥቶ ሲያሸንፈው ግን፥ ታምኖበት የነበረውን ጋሻና ጦር ይወስድበታል ምርኮውንም ያካፍላል።    (ሉቃ 11፥22) 

ሰይጣን የሚታመንበት የክፋትና የጥላቻ ጋሻና ጦር ነበረው። በሁሉም ላይ በፍቅሩ መልቶ ለመኖር ከሰማይ ወረደ ከሰማያት ሁሉ በላይ የወጣው ደግሞ ያው ነው። ይህ የወረደው ሁሉን ይሞላ ዘንድ ከሰማያት ሁሉ በላይ የወጣው ደግሞ ያው ነው ። (ኤፌ 4፥8-10)
በዓለም ላይ ሃይሎ የነበረውን ሰይጣንን አስሮታል። ተቆጣጥሮት የነበረውን ሁሉ ወስዶበታል። 

"ወይስ ሰው አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ እቃውን ሊነጥቀው እንዴት ይችላል? ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል።" (ማቴ 12 .29 )

ጌታችን እንደተናገረው ኀይለኛው ባይታሰር ኖሮ ተቆጣጥሮት የነበረውን ሁሉ መማረክ አይችልም ነበር በኀጢአታችን ላይ በርትቶ የነበረው ታስሯል ።ጌታችን ድል አድርጎ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። ዳግማኛም ይመጣል።
          ለርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን!!!

No comments:

Post a Comment