የክርስቶስ ራስነት:-
ራስ የሚለው ቃል በመፅሐፍ ቅዱስ ውሰጥ ያለው ትርጉም የነገሮች ዋና:የበላይ የሆነ:ከሁሉም ከፍ ያለ:ሁሉን ገዢ የሁሉ መሪ ማለት ነው።ታድያ ክርስቶስ ኢየሱስ የብዙ ነገር ዋናና የበላይ ነው።ይህን ስፍራ እንዲይዝ አሰቀድሞ መከራን መቀበል ቀጥሎም ወደ ክብሩ መግባት ነበረበት።
የብሉይ ኪዳን ነቢያት ይህን እውነት በአፅንዖት ተናግረዋል።ሉቃ 24:26 1ኛ ጴጥ 1:11 ይህን እውነት ሐዋርያት መሰክረዋል።ዕብ 2:18 12:2 13:12-13። እግዚአብሔር አንድያ ልጁ ኢየሱስን ያለ ልክ ከፍ ከፍ አድርጎታል።ፊሊ 2:9 በግርማዊ ዙፋን ቀኝም ጌታም ክርስቶስም አድርጎ የነገሮች ሁሉ ራስ አድርጎታል።የሐዋ 2:36 ይህ እንደ መደርደሪያ ካልን ኢየሱስ ራስ የሆነባቸው ጉዳዬች በጥቂቱ እንመልከት፦
1ኛ,ክርስቶስ ኢየሱስ የቤተክርትያን ራስ ነው።
ኤፌ 1:21-22"ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተክርስትያን ሰጠው።ክርስቶስ ሲሰቀል ሰይጣንና ዓለም ያላቸውን ኃይልና ብርታት አሳይተዋል።ያለ የሌለ ኃይል በመጠቀም ክርስቶስ ወደ መስቀለ ሞት ገፍተውታል።ይህን እንዲሆን የአይሁድ ሃይማኖትና የሮም የመንግስት ሰርዓት ተጠቅማል።ክርስቶስ የሚቃጠል መሥዋዕት ሆኖ ስለ ፅድቅና የኃጢአት መሥዋዕት ሆኖ ስለ ኃጢአት ሞተ።እግዚአብሔር ክርስቶስን ከሞት በማስነሳት የኃይሉ ብርታት አሳዬ።ከጌትነት ከአለቅነት ከኃይላትና በዓለም ከሚጠራ ስም ሁሉ በላይ እግዚአብሔር አደረገው።ለአካሉ ማለትም ለቤተክርትያንም ራስ እንደሆን ሰጠው።ቤተክርስትያን አንድ ራስ ነው ያላት እርሱም ክርስቶስ ብቻ ነው።የቤተክርስትያን head office ክርስቶስ ነው።
2ኛ,ከዚህ የቤተክርስትያን ጉዳይ ጋር ክርስቶስ የማዕዘን ድንጋይ ራስ ነው።
ኤፌ 2:20"በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኅል።የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።አማኞች ሕያዋን ድንጋይ ናቸው።1ኛ ጴጥ 2:5 እነዚህ አማኞች በክርስቶስ የማዕዘን ድንጋይ ራስነት ይገጣጠማሉ።ክርስቶስ በአማኞች ላይ የበላይ ዋና የሆነ ብቻ ሳይሆን አማኞች ሚገጣጠሙበት ነው።በእርሱ ተገጣጥመው ቅዱስ መቅደስ ይሆናሉ።
3ኛ,ክርስቶስ የህይወት ራስ።
የሐዋ 3:14-15"እናንተ ግን,,,የሕይወት ራስ ገደላችሁት እርሱን ግን እግዚአብሔር ከሙታን አስነሣው።ሰው በበደል በኃጢአት ሙት ነው።ኤፌ 2:1ነገር ግን ሰው ህይወትን ለማግኘት ወደ ክርስቶስ መምጣት አለበት።ዮሐ 17:2 ስለዚህ በስሙ ለሚያምኑ ኢየሱስ ህይወትን ይሰጣቸዋል።ምክንያቱም የህይወት ራስ ነው።ዮሐ 3:36 1ኛ ዮሐ 5:12
4ኛ,ክርስቶስ የመዳን ራስ ነው።
ዕብ 2:10"ብዙ ልጆች ወደ ክብር ያመጣ ዘንድ የመዳናቸውንም ራስ በመከራው ይፈፅም ዘንድ ለእርሱ ተገብቶታልና።ሰው መዳን የሚችል ከፍጡር ዘንድ አንድም የለም።መዳን በማንም በሌላ የለም።የሐዋ 4:12 በእርሱ(በክርስቶስ) የሚመጡትን ፈፅሞ ያድናቸዋል።ዕብ 7:23 ክርስቶስ ኃጢአተኞችን ሊያድን መጣ።1ኛ ጢም 1:15 ስለዚህ መዳንን በተመለከተ ክርስቶስ ብቻ ይመለከተዋል።ክርስቶስ የመዳናችን ዋና ነው።
5ኛ,ክርስቶስ የእምነታችን ራስ ነው።
ዕብ 12:3"የእምነታችን ራስና ፈፃሚውን ኢየሱስን ተመልከቱ።አንድ እምነት አለ።እርሱም ለቅዱሳን የተሰጠ ነው።ይሁዳ 1:3 የዚህ እምነት የበላይ ኢየሱስ ነው።ብዙ ሃይማኖቶች ራስ አላቸው። መፅሐፍ ግን ኢየሱስ የእምነታችን ራስ ነው ይለናል።አዎን ኢየሱስ ብቻ የሃይማኖት ራስ ነው።
No comments:
Post a Comment