የ2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የዘመን አቆጣጠር (ባሕረ- ሐሳብ )
“በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ” [መዝ.64(65)፥11]
▰▰▰▰▰▰▰▰▰
ዓመተ ዓለም = ዓመተ ምህረት + ዓመተ ኩነኔ (ፍዳ) = 2013 + 5500 =7513
ወንጌላዊ፦ በዓመቱ የሚሾም ወንጌላዊ ማለት ነው፡፡
ዓመተ ዓለም፥4
7513 ÷ 4 = 1878
1878 ፦ መጠነ ራብዒት ይባላል፡፡
7513 - 4×1878 = 1
ቀሪው ' 1 ' ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ማቴዎስ
ቀሪው ' 2 ' ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ማርቆስ
ቀሪው ' 3 ' ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ሉቃስ
ቀሪው ' 0 ' ከሆነ ዘመኑ ዘመነ ዮሐንስ ይሆናል።
ስለዚህ ቀሪው '1' ስለሆነ የዘንድሮው ወንጌላዊ ማቴዎስ ሲሆን ዘመኑ ዘመነ ማቴዎስ ይባላል።
•••
ዕለተ ቀመር፦ መስከረም አንድ የሚውልበት ቀን ነው፡፡
ዕለተ ቀመር= ዓመተ ዓለም+መጠነ ራብዒት÷7
= 7513 + 1878 =9391
= 9391 ÷ 7 = 1341 ቀሪ 4
ቀሪው '0 'ከሆነ ሰኞ
ቀሪው '1' ከሆነ ማክሰኞ
ቀሪው '2 'ከሆነ ረቡዕ
ቀሪው '3 'ከሆነ ሐሙስ
ቀሪው '4 'ከሆነ ዓርብ
ቀሪው '5 'ከሆነ ቅዳሜ
ቀሪው '6 'ከሆነ እሁድ መባቻ ይሆናል። በመሆኑም ዘንድሮ ቀሪው '4'ስለሆነ ዕለተ ቀመር ዓርብ ይሆናል።
•••
መደብ = ዓመተ ዓለምን በ19 በመግደፍ እናገኛለን። = 7513፥19=395 ደርሶ 8 ይቀራል። ስለዚህ መደብ 8 ይሆናል፡፡
•••
• ወንበር = ከመደብ አንድን ለዘመን በመተው ወንበርን እናገኛለን።
ወንበር =8 - 1= 7 ይሆናል።
• አበቅቴ ፦ጥንተ አበቅቴን በወንበር አባዝተን በ30 ገድፈን እናገኛለን።
አበቅቴ =11*7=77
77፥30= '2' ደርሶ ቀሪው '17' ሲሆን ዘንድሮ አበቅቴ '17'ይሆናል።
• መጥቅዕ፦ ጥንተ መጥቅዕን በወንበር አባዝተን ለ30 በመግደፍ(በማካፈል) እናገኛለን።
መጥቅዕ = 19×7 = 133
133 ÷ 30= 4 ቀሪው '13 'ስለሆነ መጥቅዕ ዘንድሮ '13 'ይሆናል።
“አበቅቴ ወመጥቅ ክሌሆሙ ኢይበዝሁ እም30 ወኢይኅዱ እም 30 ወትረ ይከዉኑ 30 ፤ አበቅቴ ቢበዛ መጥቅ ቢያንስ መጥቅ ቢበዛ አበቅቴ ቢያንስ ከ30 አይበዙም አያንሱም” ይህም ማለት በሌላ አገላለጽ መጥቅዕና አብቅቴ ተደምረዉ ዉጤቱ ከ30 መብለጥና ማነስ የለበትም፤ ሁሌ 30 ይሆናል፡፡ የዘንድሮዉ የ2013 ዓ.ም = 17+ 13 = 30።
መጥቅዕ ከ14 በላይ ከሆነ በመስከረም ይዉላል፤
መጥቅዕ ከ14 በታች ከሆነ በጥቅምት ይዉላል፤
መጥቅዕ በመስከረም ቢዉል ጾመ ነነዌ በጥር፣ መጥቅዕ በጥቅምት ቢዉል ጾመ ነነዌ በየካቲት ይብታል።
ስለዚህ በዚህ ዓመት መጥቅዕ 13 ሲሆን ከ14 ያንሳል፤ ስለዚህም መጥቅዕ በጥቅምት ይዉላል፤
•••
ስለዚህ የ2013 መጥቅዕ ጥቅምት 13 ነው ሲሆን ዕለተ መጥቅዕ አርብ ይሆናል፡፡
•••
መባጃ ሐመር፦ መጥቅዕንና የባለመጥቅዕን ተውሳክ በመደመር በ30 በመግደፍ እናገኛለን፡፡ ከዕለተ መጥቅዕ ጀምረን እስከ ነነዌ ጾም መግቢያ ስንቆጥር 128 ቀን ይሆናል፡፡ በ30 ብንገድፈዉ 4 ቀሪ 8 ይሆናል፡፡ ይህም የቅዳሜ ተውሳክ ነው። ልብ ይበሉ የዕለት ተውሳክ ከቅዳሜ ይጀምራል፡፡
• ቅዳሜ፡ 128፥30=4 ቀሪ 8
• እሁድ፡127፥30=4 ቀሪ 7
• ሰኞ፡126፥30=4 ቀሪ 6
• ማክሰኞ፡125፥30=4 ቀሪ 5
• ረቡዕ፡124 ፥30=4 ቀሪ 4
• ሐሙስ፡123፥ 30= 4 ቀሪ 3
• ዐርብ፡122፥ 30= 4 ቀሪ 2
መባጃ ሐመር=13+2=15
መባጃ ሐመር ከ30 ስለሚያንስ ራሱ 15 ይያዝና መጥቅዕ በጥቅምት ስለዋለ ጾመ ነነዌ በየካቲት 15 በዕለተ ሰኞ ይውላል ማለት ነው።
• ጾመ ነነዌ፦ መጥቅዕና የዕለቱን ተውሳክ
በመደመር በ30 ገድፈን እናገኛለን፡፡ይህ ጾም ሕጸፅ የለውም፡፡ ሌሎችን አጽዋማት ተውሳኩን ከነነዌ ደምረን ከ30 ከበለጠ ለ30 እያካፈልን እናገኛለን።
•••
፩፥ ከነነዌ ጾም እስከ ዐቢይ ጾም 14 ቀናት አሉ። ስለዚህ የዐቢይ ጾም ተውሳክ 14 ይሆናል፡፡
፪፥ ከነነዌ እስከ ደብረዘይት 41 ቀኖች አሉ፡፡
41 ÷ 30 = 1 ደርሶ ቀሪው 11 የደብረዘይት ተውሳክ ይሆናል፡፡
፫፥ ከነነዌ እስከ ሆሣዕና 62 ቀኖች አሉ፡፡
62 ÷ 30 = 2 ደርሶ ቀሪው 2 የሆሣዕና ተውሳክ ይሆናል፡፡
፬፥ ከነነዌ እስከ እስከ ስቅለት 67 ቀኖች አሉ፡፡
67 ÷ 30 = 2 ደርሶ ቀሪው 7 የስቅለት ተውሳክ ይሆናል፡፡
፭፥ ከነነዌ እስከ ትንሣኤ 69 ቀኖች አሉ፡፡
69 ÷ 30 = 2 ደርሶ ቀሪው 9 የትንሣኤ ተውሳክ ይሆናል፡፡
፮፥ ከነነዌ እስከ ርክበ ካህናት 93 ቀኖች አሉ፡፡
93 ÷ 30=3ደርሶ ቀሪው 3 የርክበ ካህናት ተውሳክ ይሆናል፡፡
፯፥ ከነነዌ እስከ ዕርገት 108 ቀኖች አሉ፡፡
108 ÷ 30 = 3 ደርሶ ቀሪው 18 የዕርገት ተውሳክ ይሆናል፡፡
፰፥ ከነነዌ እስከ ጰራቅሊጦስ 118 ቀኖች አሉ፡፡ 118 ÷ 30 = 3 ደርሶ ቀርው 28 የጰራቅሊጦስ ተውሳክ ይሆናል፡፡
፱፥ ከነነዌ እስከ ጾመ ሐዋርያት 119 ቀኖች አሉ፡፡ 119 ÷ 30 =3 ደርሶ ቀሪው 29 የጾመ ሐዋርያት ተውሳክ ነው፡፡
፲፥ ከነነዌ እስከ ጾመ ድኅነት 121 ቀኖች አሉ፡፡ 121 ÷ 30 = 4 ደርሶ ቀሪው 1 ሲሆን የጾመ ድኅነት ተውሳክ 1 ይሆናል፡፡
•••
ከዚህ ተነስተን አጽዋማትንና በዓላትን ተውሳኮቻቸውን ከነነዌ ጋር እየደመርን እናገኛለን፡፡ ስለዚህ የ2013 የነነዌ ጾም መገቢያ የካቲት 15 ይሆናል፡፡
13+2=15 ስለሆነ ነው፡፡
★ ዓብይ ጾም ተውሳኩ 14 ነው
= 14 +15= 29 ሲሆን ስለዚህ ዘንድሮ በዘመነ ማቴዎስ ዓብይ ጾም በየካቲት 29 ይገባል ማለት ነው፡፡
* ደብረ ዘይት፡ ተውሳኩ 11 ነው፡፡
11+15 =26 ይሆናል፡፡ 26 ከ 30 ስለሚያንስና በየካቲት ስላለፍን ቀጣዩን በመጋቢት እናገኛለን። ስለዚህ በመጋቢት 26 እሁድ ደብረዘይት ይሆናል።
★ ሆሣዕና ተውሳኩ 2 ነው፡፡
= 2+15 =17 ሲሆን ከ30 ስለሚያንስና በመጋቢት ስላለፍን ቀጣዩን ሚያዚያን እናገኛለን፡፡ ስለዚህ ሚያዚያ 17 እሁድ ይሆናል፡፡
★ ስቅለት ተውሳኩ 7 ነው፡፡
7+15= 22 ሲሆን ዘንድሮ በሚያዝያ 22 ዓርብ ስቅለት ይሆናል፡፡
★ ትንሣኤ ተውሳኩ 9 ነው፡፡
9 +15 = 24 ሲሆን ሚያዝያ 24 በዓለ ትንሣኤ ይውላል።
★ ርክበ ካህናት ተውሳኩ 3 ነው፡፡
3 +15 = 18 ሲሆን 18ን በሚያዝያ ስላለፍን በግንቦት 18 ረቡዕ ርክበ ካህናት ይሆናል።
★ ዕርገት ተውሳኩ 18 ነው፡፡
18 +15 = 33 ሲሆን ዘንድሮ ሰኔ 3 ሐሙስ በዓለ ዕርገት ይሆናል።
★ ጰራቅሊጦስ ተውሳኩ 28 ነው፡፡
28 +15= 43 ዚህ ሰኔ 13 እሁድ በዓለ
ጰራቅሊጦስ ይውላል።
★ ጾመ ሐዋርያት ተውሳኩ 29 ነው፡፡
29 +15=44
44 ን በ30 ገድፍን ቀሪው 14 ሲሆን ሰኔ 14 ሰኞ የሐዋርያት ጾም ይገባል።
ፆመ ድህነት ተውሳኩ 1 ነው፡፡
= 1 + 15 =16 በመሆኑም ጾመ ድህነት(የረቡዕና ዓርብ ጾም) ሰኔ 16 ይገባል።
▰▰▰▰▰▰▰▰▰
የአጽዋማትና የበዓላት ኢይወርድ ኢይዓርግ(ገደብ)
➛ጾመ ነነዌ ከጥር 17 በታች አይወርድም ፤ ከየካቲት 21 በላይ አይወጣም።
➛ ዐቢይ ጾም ከየካቲት 1 በታች አይወርድም ፤ ከመጋቢት 5 በላይ አይወጣም።
➛ ደብረዘይት ከየካቲት 28 በታች አይወርድም ፤ ከሚያዝያ 2 በላይ አይወጣም።
➛ ሆሣዕና ከመጋቢት 19 በታች አይወርድም ፤ ከሚያዝያ 23 በላይ አይወጣም።
➛ ስቅለት ከመጋቢት 24 በታች አይወርድም ፤ ከሚያዝያ 28 በላይ አይወጣም።
➛ ትንሣኤ ከመጋቢት 26 በታች አይወርድም ፤ ከሚያዝያ 30 በላይ አይወጣም።
➛ ርክበ ካህናት ከሚያዝያ 20 በታች አይወርድም ፤ ከግንቦት 24 በላይ አይወጣም።
➛ ዕርገት ከግንቦት 5 በታች አይወርድም ፤ ከሰኔ 9 በላይ አይወጣም።
▰▰▰▰▰▰▰▰▰
# ልብ_በሉ
• ጾመ ነነዌ፣ ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ሐዋርያት ከሰኞ አይወጡም።
• በዓለ ደብረዘይት፣ ሆሣዕና፣ ትንሣኤና ጰራቅሊጦስ ከእሁድ አይወጡም፡፡
• ዕርገት ከሐሙስ
• ስቅለት ከዓርብ አይወጣም።
• ርክበ ካህናትም ከረቡዕ አይወጣም።
No comments:
Post a Comment