ላከበረን መኖር
ኢየሱስ ክርስቶስ ለኃጢአታችን እንደ ሞተ እና እኛን ስለማጽደቅ እንደ ተነሳ ካመንን እና በዚህ እምነት የተቀበልነውን ስልጣን መጠቀም ከጀመርን የሚጠበቅብን ላከበረን ክብር መኖር ነው፡፡ እኛ እንድንከብር የተዋረደ አለ፤ እኛ በነፃ እንድንለቀቅ የታሰረ አለ፤ እኛ እንድንለብስ የተራቆተ አለ፤ እኛ እንድናርፍ ያቃሰተ አለ፡፡ እርሱም፡- ጻድቅ የሆነው ኢየሱስ ነው፡፡ እንዲህ ሆኖ ላከበረን ለእርሱ መኖር አለብን፡፡
እኛ የራሳችን አይደለንም፤ በደም ዋጋ የገዛን አለ፡፡ 1ቆሮ 6፡20፡፡ ላከበረን መኖር መጀመር አለብን፡፡ “በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ።” እንደተባለ፡፡ 2ቆሮ 5፡15፡፡ እኛ እና ዓለማችን ለክብሩ መንበርከክ አለብን፡፡ በእኛ ላይ በሚሰራው የእግዚአብሔር ኃይል በዙሪያችን መልካም ተጽዕኖ ማምጣት አለብን፡፡
የራሳችንንም የሌሎችንም ሕይወት ውብ በማድረግ አባታችንን እናስከብር፡፡ መብላታችን እና መጠጣታችን አንኳን ሳይቀር ለክብሩ እዲሆን ይፈለጋል፡፡ “እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።” 1ቆሮ 10፡31፡፡ እያንዳንዱ የኑሯችን ገጽ አዳኛችንን መተረክ አለበት፡፡ ለራሳችን የሮጥንበት ዘመን ይብቃ እና ደግሞ ላከበረን እንኑር፡፡
ወስብሀት ለእግዚአብሔር!!!
No comments:
Post a Comment